የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ክልሉ ከ10 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ፈቃድ ሰጠ

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ሥድስት ወራት 10 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሰጠ።

የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አባስ መሐመድ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት÷ ፈቃድ የተሰጣቸው 146 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ናቸው።

ከእነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል 26ቱ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ያስመዘገቡ የዳያስፖራ ባለሃብቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአጠቃላይ ፈቃድ የተሰጠባቸው ዘርፎችም ግብርና፣ አገልግሎት እና ኢንዱስትሪ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቶቹ ወደ ሥራ ሲገቡ ለ21 ሺህ 679 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጠር ይጠበቃል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ፈቃድ ያወጡ ፕሮጀክቶች ያስመዘገቡት ካፒታል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 95 ቢሊየን ብር ብልጫ ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።

በሌላ በኩል የተረከቡትን መሬት በአግባቡ ባላለሙ 40 ፕሮጀክቶች ላይ የተለያየ ደረጃ ያለው ርምጃ መወሰዱን አስረድተዋል።

በዚህም መሠረት 33 ማስጠንቀቂያ እንዲሁም ሰባት ፕሮጀክቶች ላይ ደግሞ ውልና የኢንቨስትመንት ፈቃድ የመሰረዝ ርምጃ መወሰዱን ነው ያስረዱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026