🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ሥድስት ወራት 10 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሰጠ።
የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አባስ መሐመድ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት÷ ፈቃድ የተሰጣቸው 146 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ናቸው።
ከእነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል 26ቱ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ያስመዘገቡ የዳያስፖራ ባለሃብቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ፈቃድ የተሰጠባቸው ዘርፎችም ግብርና፣ አገልግሎት እና ኢንዱስትሪ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ፕሮጀክቶቹ ወደ ሥራ ሲገቡ ለ21 ሺህ 679 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጠር ይጠበቃል ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ፈቃድ ያወጡ ፕሮጀክቶች ያስመዘገቡት ካፒታል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 95 ቢሊየን ብር ብልጫ ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።
በሌላ በኩል የተረከቡትን መሬት በአግባቡ ባላለሙ 40 ፕሮጀክቶች ላይ የተለያየ ደረጃ ያለው ርምጃ መወሰዱን አስረድተዋል።
በዚህም መሠረት 33 ማስጠንቀቂያ እንዲሁም ሰባት ፕሮጀክቶች ላይ ደግሞ ውልና የኢንቨስትመንት ፈቃድ የመሰረዝ ርምጃ መወሰዱን ነው ያስረዱት።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026