የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአስተዳደሩ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት የሚያሳልጥ የቴክኖሎጂ አሰራር አቅም ተገንብቷል

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት የሚያሳልጥ የቴክኖሎጂ አሰራር አቅም መገንባቱን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ።

‎በአዲስ አበባ ከተማ 23 ወረዳዎች በኃይል መቆራረጥ የሚፈጠርን የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተት ምላሽ የሚሰጥ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።

‎በዚሁ ጊዜ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፤ የመዲናዋን ነዋሪዎች የተቋማት የአገልግሎት ፍላጎት እርካታ የሚያረጋግጥ ዘመናዊ አሰራር እየተዘረጋ ነው ብለዋል።


በዚህም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፈጠረው ዘመናዊ የቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓት አቅም ለተገልጋዮች የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማሳለጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎በወረዳዎች የተገነባው የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክትም በኃይል መቆራረጥ ምክንያት የሚፈጠርን የአገልግሎት ክፍተት ምላሽ በመስጠት የደንበኛ እርካታን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

በተለይም በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ወቅት የኤሌክትሪክ ኃይል ሲቋረጥ ለሚፈጠሩ የአገልግሎት ክፍተቶች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ለደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚረዳ አስረድተዋል።

በቀጣይም የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች በአስተማማኝ የኃይል አቅርቦትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ አሰራር የማስቀጠል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ፤ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቱ የወሳኝ ኩነት አገልግሎቶችን ለማሳለጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብለዋል።

በቀጣይም አገልግሎት በሚበዛባቸው ወረዳዎች የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቶችን በማስፋት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲያገኙ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።


የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እሸቱ ለማ (ዶ/ር)፤ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቱ በኃይል መቆራረጥ ምክንያት የሚፈጥርን የአገልግሎት ክፍተት አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንደሚረዳ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026