የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ዘመናዊ አኗኗርን መሰረት ያደረጉ መኖሪያ ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቷል - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ ዘመናዊ አኗኗርን መሰረት ያደረጉ መኖሪያ ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።

ክልላዊ የተቀናጀ የገጠር ማዕከላት የቤት ልማት የንቅናቄ መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በወቅቱ እንደገለፁት በከተማም ሆነ በገጠር ዘመኑን የሚመጥኑ፣ ለኑሮ የሚመቹ ቤቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ወቅቱ የሚጠይቀው ተግባር ነው።


የቤት አቅርቦት ችግርን በመፍታት ዘመናዊ ቤቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ የኢኮኖሚ ችግር መፍታት ብቻ ሳይሆን ማህበራዊ ፍትህን ማረጋገጥ ጭምር መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም ከፌዴራል የቤት አቅርቦት ፖሊሲ ጋር የተናበበና የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገባ የቤት መሰረተ ልማትን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

የገጠር ቤት ልማትና ደረጃን በማሳደግ ወደ ከተማ የሚፈልሰውን የሰው ሃይል ለመቀነስና ሀብት የሚፈጥርበትን እንዲሁም ዘመናዊ አኗኗርን የሚላመድበት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለዚህም አመራሩ የህብረተሰቡን የመኖርያ ቤት እጥረት ለመፍትት በገጠርም ሆነ በከተማ ዘመናዊ አኗኗርን መሰረት ያደረጉ መኖሪያ ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።

የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ የገጠር ኮሪደር ልማትን ተደራሽ ማድረግ፣ ሁሉን አካታች የገጠር ማዕከላትን ማስፋት፣ በከተሞች የቤት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ለተግባራዊነቱም ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።


የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሞላ መልካሙ(ዶ/ር) በበኩላቸው የገጠር ማዕከላትንና አካታች መንደሮችን በማስፋት የህብረተሰቡን ኑሮ ለማቃለል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የከተማ ቤት አቅርቦት ችግርን ከመቅረፍ ባለፈ የገጠር ቤቶችን ዘመኑን የዋጁ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም የክልሉ መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025