🔇Unmute
ባህርዳር፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ ዘመናዊ አኗኗርን መሰረት ያደረጉ መኖሪያ ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።
ክልላዊ የተቀናጀ የገጠር ማዕከላት የቤት ልማት የንቅናቄ መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።
ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በወቅቱ እንደገለፁት በከተማም ሆነ በገጠር ዘመኑን የሚመጥኑ፣ ለኑሮ የሚመቹ ቤቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ወቅቱ የሚጠይቀው ተግባር ነው።

የቤት አቅርቦት ችግርን በመፍታት ዘመናዊ ቤቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ የኢኮኖሚ ችግር መፍታት ብቻ ሳይሆን ማህበራዊ ፍትህን ማረጋገጥ ጭምር መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ከፌዴራል የቤት አቅርቦት ፖሊሲ ጋር የተናበበና የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገባ የቤት መሰረተ ልማትን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
የገጠር ቤት ልማትና ደረጃን በማሳደግ ወደ ከተማ የሚፈልሰውን የሰው ሃይል ለመቀነስና ሀብት የሚፈጥርበትን እንዲሁም ዘመናዊ አኗኗርን የሚላመድበት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ለዚህም አመራሩ የህብረተሰቡን የመኖርያ ቤት እጥረት ለመፍትት በገጠርም ሆነ በከተማ ዘመናዊ አኗኗርን መሰረት ያደረጉ መኖሪያ ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።
የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ የገጠር ኮሪደር ልማትን ተደራሽ ማድረግ፣ ሁሉን አካታች የገጠር ማዕከላትን ማስፋት፣ በከተሞች የቤት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ለተግባራዊነቱም ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሞላ መልካሙ(ዶ/ር) በበኩላቸው የገጠር ማዕከላትንና አካታች መንደሮችን በማስፋት የህብረተሰቡን ኑሮ ለማቃለል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የከተማ ቤት አቅርቦት ችግርን ከመቅረፍ ባለፈ የገጠር ቤቶችን ዘመኑን የዋጁ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም የክልሉ መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026