የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አርሶ አደሮች በለሙ ተፋሰሶች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተሰማርተው ተጠቃሚ ሆነዋል

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ቀደም ሲል የለሙ ተፋሰሶች ለሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በፈጠሩት ምቹ መደላድል ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ።

የዞኑ አርሶ አደሮች በመርሃግብሩ ታግዘው በንብ ማነብ፣ በወተት ላም እርባታ፣ በእንስሳት ማድለብ እንዲሁም በአቮካዶ ተክልና በቡና ልማት በመሰማራት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን ተናግረዋል፡፡

በዞኑ የላይ አርማጭሆ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር እሸቴ ንብረት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ባገገሙ ተፋሰሶች በቡና ልማት ተሰማርተው ከምርት ሽያጭ በዓመት እስከ 80ሺህ ብር ገቢ እያገኙ ነው፡፡


ያገገሙ ተፋሰሶች ለአርሶ አደሩ የሀብት ምንጭ እየሆኑ መጥተዋል ያሉት አርሶ አደሩ ለልጆቻችን ጭምር የሥራ ዕድል በመፍጠር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንድንሆን አስችሎናል ብለዋል፡፡

የአለፋ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር በላይ መንግስቴ በበኩላቸው፤ በሌማት ትሩፋት መርሃግብር በንብ ማነብ ሥራ ተሰማርተው አሁን ላይ ከ40 የንብ ቀፎዎች ማር እያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


በለሙ ተፋሰሶች እያከናወኑት ባለው የንብ ማነብ ሥራ ከአንድ የንብ ቀፎ እስከ 15 ኪሎ ግራም ማር በመሰብሰብና አንዱን ኪሎ በ600 ብር በመሸጥ ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

በለሙ ተፋሰሶች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የወተት ላም እርባታ ሥራ መጀመራቸውን የገለጹት ደግሞ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ የምንዝሮ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር በሪሁን ታከለ ናቸው፡፡


ተፋሰሱ ለእንስሳት መኖ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና ካሏቸው ሦስት የወተት ላሞች በቀን የሚያገኙት 24 ሊትር ወተት ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ በበኩላቸው፤ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በህብረተሰቡ ተሳትፎ በተከናወነ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራ የለሙ አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሪያና የሀብት ምንጭ እየሆኑ ነው፡፡


የለሙ ተፋሰሶች ለሌማት ትሩፋት መርሀግብር ትግበራ ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን ጠቁመው፣ በዚህም አርሶ አደሩ የምግብ ሉአላዊነቱን እንዲያረጋግጥና ሀብት እንዲያፈራ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።

ያለፉትን ዓመታት ተሞክሮ በመቀመር በዘንድሮ የበጋ ወራት በዞኑ 15 ወረዳዎች የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት መጀመሩን የተናገሩት ሃላፊው በዚህም 52 ሺህ ሄክታር የሚሸፍን የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ይከናወናል ሲሉ ገልጸዋል።

እንደ አቶ ንጉሴ ገለጻ ለ35 ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ከ467 ሺህ በላይ ነዋሪዎች በልማት ቡድኖች ተደራጅተው ይሳተፋሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026