የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አርሶ አደሮች በለሙ ተፋሰሶች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተሰማርተው ተጠቃሚ ሆነዋል

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ቀደም ሲል የለሙ ተፋሰሶች ለሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በፈጠሩት ምቹ መደላድል ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ።

የዞኑ አርሶ አደሮች በመርሃግብሩ ታግዘው በንብ ማነብ፣ በወተት ላም እርባታ፣ በእንስሳት ማድለብ እንዲሁም በአቮካዶ ተክልና በቡና ልማት በመሰማራት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን ተናግረዋል፡፡

በዞኑ የላይ አርማጭሆ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር እሸቴ ንብረት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ባገገሙ ተፋሰሶች በቡና ልማት ተሰማርተው ከምርት ሽያጭ በዓመት እስከ 80ሺህ ብር ገቢ እያገኙ ነው፡፡


ያገገሙ ተፋሰሶች ለአርሶ አደሩ የሀብት ምንጭ እየሆኑ መጥተዋል ያሉት አርሶ አደሩ ለልጆቻችን ጭምር የሥራ ዕድል በመፍጠር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንድንሆን አስችሎናል ብለዋል፡፡

የአለፋ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር በላይ መንግስቴ በበኩላቸው፤ በሌማት ትሩፋት መርሃግብር በንብ ማነብ ሥራ ተሰማርተው አሁን ላይ ከ40 የንብ ቀፎዎች ማር እያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


በለሙ ተፋሰሶች እያከናወኑት ባለው የንብ ማነብ ሥራ ከአንድ የንብ ቀፎ እስከ 15 ኪሎ ግራም ማር በመሰብሰብና አንዱን ኪሎ በ600 ብር በመሸጥ ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

በለሙ ተፋሰሶች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የወተት ላም እርባታ ሥራ መጀመራቸውን የገለጹት ደግሞ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ የምንዝሮ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር በሪሁን ታከለ ናቸው፡፡


ተፋሰሱ ለእንስሳት መኖ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና ካሏቸው ሦስት የወተት ላሞች በቀን የሚያገኙት 24 ሊትር ወተት ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ በበኩላቸው፤ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በህብረተሰቡ ተሳትፎ በተከናወነ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራ የለሙ አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሪያና የሀብት ምንጭ እየሆኑ ነው፡፡


የለሙ ተፋሰሶች ለሌማት ትሩፋት መርሀግብር ትግበራ ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን ጠቁመው፣ በዚህም አርሶ አደሩ የምግብ ሉአላዊነቱን እንዲያረጋግጥና ሀብት እንዲያፈራ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።

ያለፉትን ዓመታት ተሞክሮ በመቀመር በዘንድሮ የበጋ ወራት በዞኑ 15 ወረዳዎች የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት መጀመሩን የተናገሩት ሃላፊው በዚህም 52 ሺህ ሄክታር የሚሸፍን የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ይከናወናል ሲሉ ገልጸዋል።

እንደ አቶ ንጉሴ ገለጻ ለ35 ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ከ467 ሺህ በላይ ነዋሪዎች በልማት ቡድኖች ተደራጅተው ይሳተፋሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026