የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ ለዲጂታል ዲፕሎማሲ ልዩ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዘመኑን የቴክኖሎጂ ውጤቶች በመጠቀም የሀገርን ገጽታ ለማስተዋወቅ እንዲሁም ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ ለዲጂታል ዲፕሎማሲ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲጂታል ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ስላባት ማናዬ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ዲጂታል ዲፕሎማሲ የአንድን ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ በስትራቴጂያዊ መንገድ ጥቅም ላይ እየዋለ የሚገኝ ወሳኝ መሣሪያ ነው ብለዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የተተገበረው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ለዲጂታል ዲፕሎማሲ ስራ ምቹ ምህዳር መፍጠሩንም አስታውሰዋል።

ዳይሬክተሩ አክለውም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ላይ ትኩረት የሚያደርግ በመሆኑ ለዘርፉ ትልቅ ዕድል ይዞ እንደሚመጣ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የአፍሪካ የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የምታደርገው ጉዞ ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ የሚደግፍ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በቀጣይ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንሲ አማካኝነት ተገልጋዮች ወደ ቆንስላዎች በአካል መሄድ ሳያስፈልጋቸው በስልካቸው አገልግሎት የሚያገኙበት አሰራር እንደሚዘረጋም ጠቁመዋል።

በህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጉብኝት ወቅት ይፋ የተደረገው የዳታ ማዕከል ግንባታም ዲጂታል ዲፕሎማሲውን ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ነው የተናገሩት።

ኢትዮጵያ በሁለትዮሽና በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ያላትን ተመራጭነት አንስተውም፤ ሀገሪቱ ለመካከለኛው ምስራቅ፣ ለእስያና ለአውሮፓ ያላት አማካይ መገኛ እና ለቀይ ባህር ያላት ቅርበት ሁነኛ የዲፕሎማሲ አጋር ያደርጋታል ብለዋል።

የቱሪዝም ዲፕሎማሲ ስራም በዲጂታል ዲፕሎማሲ በኩል እየተከናወነ እንደሚገኝ ጨምረው ገልፀዋል።

ለዚህም ተፈጥሯዊና ስትራቴጂያዊ ጸጋዎች እንዲሁም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተገነቡት የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዲጂታል አማራጮች ለዓለም የማስተዋወቅ ስራን በአብነት ጠቅሰዋል።

21ኛው ክፍለ ዘመን የትርክት የበላይነትን ለመቆጣጠር የሚደረግ የመረጃ ውድድር ያየለበት ወቅት መሆኑንም ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።

በሚቀያየረው የቴክኖሎጂ አውድ ውስጥ ተዋናይ ለመሆን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መረጃን በዲጂታል ዲፕሎማሲው በመተንተንና ቀድሞ በመተንበይ ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም መከበር ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025