የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

መተግበሪያው አገልግሎትን ለማቀላጠፍና ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከል ትልቅ ፋይዳ አለው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይፋ ያደረገው መተግበሪያ ዳያስፖራው ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ ገለጹ።

‎የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 'CBE Connect Digital Wallet' የተሰኘ ከውጭ ሀገር ገንዘብ ለመላክ የሚያስችል አዲስ መተግበሪያ ስራ አስጀምሯል።


‎‎የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ላይ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ባንኩ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በስኬት መሻገሩን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ለሚደረገው ጉዞ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡

‎ዛሬ ይፋ የተደረገው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዲያስፖራው ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ ከማስቻሉም ባለፈ፣ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከልና የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ግኝት ለማሳደግ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት ተወካይና የኮርፖሬት አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ኤፍሬም መኩሪያ በበኩላቸው፤ ባንኩ በየወቅቱ አሰራሩን በማዘመን ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ባንኩ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት ላይ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

ስራ ላይ የዋለው መተግበሪያ የባንኩን የዲጂታል ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ጠቅሰው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ደንበኞችን ይበልጥ የሚያስተሳስርና የሐዋላ ሂደትን የሚያቀላጥፍ መሆኑን ተናግረዋል።

መተግበሪያው በኢትዮጵያ የፋይናንስ ስርዓት ባለው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን መተግበሪያውን ከንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ያበለጸገው የስታር ፔይ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሱፍቃድ ጌታቸው ገልጸዋል።


‎‎መንግስት ለቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የፈጠረው ምቹ ሁኔታ መሰል ፈጠራዎች እንዲበራከቱ ማድረጉን ጠቅሰው፣ በቀጣይም ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለማበልጸግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026