🔇Unmute
ነገሌ ቦረና፤ ጥር 14/2018 (ኢዜአ)፡- የግብር ከፋዩ ግንዛቤ በማደጉና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር በመተግበሩ የተሻለ ገቢ መሰብሰቡን የምሥራቅ ቦረና ዞን ገቢዎች ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
በጽሕፈት ቤቱ የዕቅድ፣ በጀት ክትትልና ግምገማ ባለሙያ መዓዛ አሊ እንዳሉት፤ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን አሟጦ ለመጠቀም የግብር ከፋዩን ግንዛቤ የማሳደግ ሥራ በትኩረት ሲሠራ ቆይቷል።
የገቢ አሰባሰቡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ መደረጉም የገቢ ዐቅምን ማሳደግ ማስቻሉን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ከ854 ሚሊየን 528 ሺህ ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቅሰዋል።
አፈጻጸሙ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ341 ሚሊየን 502 ሺህ ብር ብልጫ እንዳለውም ለኢዜአ ተናግረዋል።
በነገሌ ቦረና ከተማ በሆቴል ንግድ የተሰማሩት አመለወርቅ ክፍሌ እንዳሉት፤ ዐቅምን ያገናዘበ የግብር ውሳኔ መሰጠቱ ነጋዴው ግብሩን ያለቅሬታ እንዲከፍልና ዜጎች የተሟላ መንግሥታዊ አገልግሎት እንዲያገኙ አስችሏል።

በሸቀጣ ሸቀጥ ንግድ ሥራ የተሰማሩት ቢኒያም ተፈራ በበኩላቸው፤ ግብርን በወቅቱ በመክፈል ሕግና ሥርዓትን ማክበር እንዲሁም ፍትሐዊ የንግድ ውድድርን ማስፈን የነጋዴው ግዴታ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የሀገር ልማትን ለማስቀጠል ግብር የመክፈል ግዴታ የተጣለበት ዜጋ ሁሉ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ያስረዱት ደግሞ ሌላኛዋ ግብር ከፋይ ብርቅነሽ ገብረሚካኤል ናቸው።

በታማኝነት ግብር በመክፈል ሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ማስቆምና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን ሲሉም አስተያየት ሰጭዎቹ በአጽንኦት ገልጸዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026