የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር መተግበሩ የተሻለ ገቢ እንዲሰበሰብ አስችሏል

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነገሌ ቦረና፤ ጥር 14/2018 (ኢዜአ)፡- የግብር ከፋዩ ግንዛቤ በማደጉና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር በመተግበሩ የተሻለ ገቢ መሰብሰቡን የምሥራቅ ቦረና ዞን ገቢዎች ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

በጽሕፈት ቤቱ የዕቅድ፣ በጀት ክትትልና ግምገማ ባለሙያ መዓዛ አሊ እንዳሉት፤ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን አሟጦ ለመጠቀም የግብር ከፋዩን ግንዛቤ የማሳደግ ሥራ በትኩረት ሲሠራ ቆይቷል።

የገቢ አሰባሰቡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ መደረጉም የገቢ ዐቅምን ማሳደግ ማስቻሉን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ከ854 ሚሊየን 528 ሺህ ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቅሰዋል።

አፈጻጸሙ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ341 ሚሊየን 502 ሺህ ብር ብልጫ እንዳለውም ለኢዜአ ተናግረዋል።

በነገሌ ቦረና ከተማ በሆቴል ንግድ የተሰማሩት አመለወርቅ ክፍሌ እንዳሉት፤ ዐቅምን ያገናዘበ የግብር ውሳኔ መሰጠቱ ነጋዴው ግብሩን ያለቅሬታ እንዲከፍልና ዜጎች የተሟላ መንግሥታዊ አገልግሎት እንዲያገኙ አስችሏል።


በሸቀጣ ሸቀጥ ንግድ ሥራ የተሰማሩት ቢኒያም ተፈራ በበኩላቸው፤ ግብርን በወቅቱ በመክፈል ሕግና ሥርዓትን ማክበር እንዲሁም ፍትሐዊ የንግድ ውድድርን ማስፈን የነጋዴው ግዴታ መሆኑን አስገንዝበዋል።


የሀገር ልማትን ለማስቀጠል ግብር የመክፈል ግዴታ የተጣለበት ዜጋ ሁሉ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ያስረዱት ደግሞ ሌላኛዋ ግብር ከፋይ ብርቅነሽ ገብረሚካኤል ናቸው።


በታማኝነት ግብር በመክፈል ሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ማስቆምና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን ሲሉም አስተያየት ሰጭዎቹ በአጽንኦት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025