🔇Unmute
ነገሌ ቦረና፤ ጥር 14/2018 (ኢዜአ)፡- የግብር ከፋዩ ግንዛቤ በማደጉና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር በመተግበሩ የተሻለ ገቢ መሰብሰቡን የምሥራቅ ቦረና ዞን ገቢዎች ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
በጽሕፈት ቤቱ የዕቅድ፣ በጀት ክትትልና ግምገማ ባለሙያ መዓዛ አሊ እንዳሉት፤ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን አሟጦ ለመጠቀም የግብር ከፋዩን ግንዛቤ የማሳደግ ሥራ በትኩረት ሲሠራ ቆይቷል።
የገቢ አሰባሰቡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ መደረጉም የገቢ ዐቅምን ማሳደግ ማስቻሉን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ከ854 ሚሊየን 528 ሺህ ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቅሰዋል።
አፈጻጸሙ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ341 ሚሊየን 502 ሺህ ብር ብልጫ እንዳለውም ለኢዜአ ተናግረዋል።
በነገሌ ቦረና ከተማ በሆቴል ንግድ የተሰማሩት አመለወርቅ ክፍሌ እንዳሉት፤ ዐቅምን ያገናዘበ የግብር ውሳኔ መሰጠቱ ነጋዴው ግብሩን ያለቅሬታ እንዲከፍልና ዜጎች የተሟላ መንግሥታዊ አገልግሎት እንዲያገኙ አስችሏል።

በሸቀጣ ሸቀጥ ንግድ ሥራ የተሰማሩት ቢኒያም ተፈራ በበኩላቸው፤ ግብርን በወቅቱ በመክፈል ሕግና ሥርዓትን ማክበር እንዲሁም ፍትሐዊ የንግድ ውድድርን ማስፈን የነጋዴው ግዴታ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የሀገር ልማትን ለማስቀጠል ግብር የመክፈል ግዴታ የተጣለበት ዜጋ ሁሉ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ያስረዱት ደግሞ ሌላኛዋ ግብር ከፋይ ብርቅነሽ ገብረሚካኤል ናቸው።

በታማኝነት ግብር በመክፈል ሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ማስቆምና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን ሲሉም አስተያየት ሰጭዎቹ በአጽንኦት ገልጸዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026