የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ የፍራፍሬ ልማትን ለማስፋት የችግኝ ዝግጅት እየተከናወነ ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦በኢሉአባቦር ዞን በኢኒሼቲቭ መልክ እየተተገበረ የሚገኘውን የፍራፍሬ ልማት ለማስፋት የችግኝ ዝግጅት በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

የኢሉአባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቻላቸው አዱኛ፣ በዞኑ በኢኒሼቲቭ መልክ አቮካዶ፣ ሙዝና ፓፓያ በስፋት እየለማ ይገኛል ብለዋል።

በዞኑ ከ32 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት ላይ የፍራፍሬ ልማት እየተከናወነ ሲሆን ከሚለማው መሬት ውስጥ 28 ሺህ ሔክታር ላይ የሚገኘው ምርት መስጠት መጀመሩን ገልጸዋል።


ስራውን የበለጠ ለማፋፋትም በ220 የመንግስት የችግኝ ጣቢያዎችና በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ የችግኝ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም ምርታማነታቸው ከፍተኛ የሆኑ ከግብርና ምርምር የወጡ የአቮካዶ፣ የሙዝና የሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች የተዘጋጁ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

በችግኝ ማፍላት ስራው ከ42 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውንም አክለዋል።

በበጋው ወራት የተዘጋጁት እነዚህን ችግኞች በተቀናጀ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በተሰራበት መሬት ላይ እንደሚተከሉም ገልጸዋል።


ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚሰጡት እነዚህ ችግኞች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እንደሚያግዙም አስረድተዋል።

ጥምር ጥቅም በሚሰጡ ችግኝ ማፍላት ከተሰማሩ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ በሁሩሙ ወረዳ የሎኮ ሳያ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ተካልኝ ታደገ እንዳሉት፤ አቮካዶና ሙዝ በማምረት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ ነው።


ስራውንም የዛሬ ሁለት ዓመት በበጋ ወራት በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት በተከናወነባቸው ሩብ ሔክታር መሬታቸው ላይ በመተግባር መጀመራቸውን አስታውሰዋል።

የፍራፍሬ ግብርናው በትንሽ ማሳ ላይ የምግብ ዋስትናና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ አቅም እንደሆናቸው አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026