🔇Unmute
መቱ ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦በኢሉአባቦር ዞን በኢኒሼቲቭ መልክ እየተተገበረ የሚገኘውን የፍራፍሬ ልማት ለማስፋት የችግኝ ዝግጅት በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።
የኢሉአባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቻላቸው አዱኛ፣ በዞኑ በኢኒሼቲቭ መልክ አቮካዶ፣ ሙዝና ፓፓያ በስፋት እየለማ ይገኛል ብለዋል።
በዞኑ ከ32 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት ላይ የፍራፍሬ ልማት እየተከናወነ ሲሆን ከሚለማው መሬት ውስጥ 28 ሺህ ሔክታር ላይ የሚገኘው ምርት መስጠት መጀመሩን ገልጸዋል።

ስራውን የበለጠ ለማፋፋትም በ220 የመንግስት የችግኝ ጣቢያዎችና በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ የችግኝ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም ምርታማነታቸው ከፍተኛ የሆኑ ከግብርና ምርምር የወጡ የአቮካዶ፣ የሙዝና የሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች የተዘጋጁ መሆናቸውን ነው የገለጹት።
በችግኝ ማፍላት ስራው ከ42 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውንም አክለዋል።
በበጋው ወራት የተዘጋጁት እነዚህን ችግኞች በተቀናጀ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በተሰራበት መሬት ላይ እንደሚተከሉም ገልጸዋል።

ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚሰጡት እነዚህ ችግኞች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እንደሚያግዙም አስረድተዋል።
ጥምር ጥቅም በሚሰጡ ችግኝ ማፍላት ከተሰማሩ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ በሁሩሙ ወረዳ የሎኮ ሳያ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ተካልኝ ታደገ እንዳሉት፤ አቮካዶና ሙዝ በማምረት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ ነው።

ስራውንም የዛሬ ሁለት ዓመት በበጋ ወራት በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት በተከናወነባቸው ሩብ ሔክታር መሬታቸው ላይ በመተግባር መጀመራቸውን አስታውሰዋል።
የፍራፍሬ ግብርናው በትንሽ ማሳ ላይ የምግብ ዋስትናና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ አቅም እንደሆናቸው አንስተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025