የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ የፍራፍሬ ልማትን ለማስፋት የችግኝ ዝግጅት እየተከናወነ ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦በኢሉአባቦር ዞን በኢኒሼቲቭ መልክ እየተተገበረ የሚገኘውን የፍራፍሬ ልማት ለማስፋት የችግኝ ዝግጅት በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

የኢሉአባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቻላቸው አዱኛ፣ በዞኑ በኢኒሼቲቭ መልክ አቮካዶ፣ ሙዝና ፓፓያ በስፋት እየለማ ይገኛል ብለዋል።

በዞኑ ከ32 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት ላይ የፍራፍሬ ልማት እየተከናወነ ሲሆን ከሚለማው መሬት ውስጥ 28 ሺህ ሔክታር ላይ የሚገኘው ምርት መስጠት መጀመሩን ገልጸዋል።


ስራውን የበለጠ ለማፋፋትም በ220 የመንግስት የችግኝ ጣቢያዎችና በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ የችግኝ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም ምርታማነታቸው ከፍተኛ የሆኑ ከግብርና ምርምር የወጡ የአቮካዶ፣ የሙዝና የሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች የተዘጋጁ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

በችግኝ ማፍላት ስራው ከ42 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውንም አክለዋል።

በበጋው ወራት የተዘጋጁት እነዚህን ችግኞች በተቀናጀ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በተሰራበት መሬት ላይ እንደሚተከሉም ገልጸዋል።


ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚሰጡት እነዚህ ችግኞች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እንደሚያግዙም አስረድተዋል።

ጥምር ጥቅም በሚሰጡ ችግኝ ማፍላት ከተሰማሩ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ በሁሩሙ ወረዳ የሎኮ ሳያ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ተካልኝ ታደገ እንዳሉት፤ አቮካዶና ሙዝ በማምረት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ ነው።


ስራውንም የዛሬ ሁለት ዓመት በበጋ ወራት በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት በተከናወነባቸው ሩብ ሔክታር መሬታቸው ላይ በመተግባር መጀመራቸውን አስታውሰዋል።

የፍራፍሬ ግብርናው በትንሽ ማሳ ላይ የምግብ ዋስትናና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ አቅም እንደሆናቸው አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026