🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ከአህጉራዊ ራዕይ ባለፈ የዜጎችን ኑሮ የሚቀይር ፕሮጀክት ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አሳሰቡ።
የአጀንዳ 2063 ትግበራ የሚከታተለው የሚኒስትሮች ኮሚቴ ዛሬ ስብሰባውን በበይነ መረብ አድርጓል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት አዲሱ የህብረቱ አመራር አጀንዳ 2063 ውጤታማ ለማድረግ ከቃል የተሻገረ የፖለቲካ ቁርጠኝነትን በመላበስ አበክሮ መስራት ይገባዋል።
የአጀንዳ 2063 የ10 ዓመት የሁለተኛ ምዕራፍ የትግበራ እቅድ አህጉራዊውን ማዕቀፍ ለማፋጠን የሚያስችል ግልጽ ፍኖተ ካርታ እንዳለው አመልክተዋል።
ይሁንና አነስተኛ የፋይናንስ አቅርቦት፣ የትላልቅ ፕሮጀክቶች መጓተት እና የተቋማዊ አቅም ውስንነት የሚፈለገውን ውጤት አለማስገኘቱን ተናግረዋል።
ሊቀ መንበሩ ራዕይን ከፋይናንስ አቅርቦት፣ እቅድን የመፈጸም አቅምን ከመጨመር እና ክትትልን ከተጠያቂነት ጋር ማስተሳሰር ይገባል ነው ያሉት።
የአስተዳደር ሪፎርሞች ማጠናከር እና የፖሊሲ ማነቆዎችን ማስቀረት ቁልፍ እንደሆነም አንስተዋል።
የአፍሪካ ሀገራት ከአጀንዳ 2063ትንየአፍሪካውያን የዕለት ተዕለት ኑሮ ወደ መቀየር ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ሊቀ መንበሩ ማሳሰባቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025