🔇Unmute
አጋሮ፤ ጥር 29/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊና ግልጽ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እያገዘ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር) ገለጹ።
የአጋሮ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬ በይፋ ስራ ጀምሯል።
በማስጀመሪያ መድረኩ የተገኙት ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር)፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በየአካባቢው ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ግልጽ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እያገዘ ነው ብለዋል።
የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ የመልካም አስተዳደር ችግርን ትርጉም ባለው መልኩ መፍታት እያስቻለና በተለይም የህዝቡን እንግልት ለመቀነስና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ እንደሚጠናከር ገልጸዋል።
በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ በበኩላቸው የክልሉ መንግስት ሕዝቡ ለረጅም ጊዜ ሲያነሳ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ ነው።
ከእነዚህ ስራዎች መካከል አንዱ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መሆኑን ጠቅሰው እስካሁንም በሸገር፣ በአዳማ፣ በጅማ፣ በቢሾፍቱ እና በሻሸመኔ ከተሞች መጀመሩን አስታውሰዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀድሞ በተጀመረባቸው ከተሞች አገልግሎቱ የበለጠ እየሰፋ ወደ ክፍለ ከተሞችም እየወረደ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጋሮ ከተማ አስተዳደር የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ዘመናዊ እና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እድል ይፈጥራል ብለዋል።
የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ስራ መጀመር በከተማ አስተዳደሩ ሲነሳ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የሚያግዝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአጋሮ ከተማ ከንቲባ ነዚፍ መሀመድ አሚን ናቸው።
የአንድ ማዕከል አገልግሎቱን ወደ ስራ ለማስገባት ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026