የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ የፋይናንስ ስርአቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል እየተሰራ ነው

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ከሚሴ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):- በአማራ ክልል የፋይናንስ ስርአቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠንና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በከሚሴ ከተማ እያካሄደ ነው።

የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን እንደገለፁት፣ የክልሉን ገቢና ወጭ በማጣጣም ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው።


ለዚህም የፋይናንስ አጠቃቀምን ዲጂታላይዝ በማድረግ በሀብት አጠቃቀምና በሌሎችም አበረታች ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።

በተለይም በመንግስት ግዥ፣ በውስጥ ኦዲት፣ በወጪ አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጡ ግልጸኝነት ያለው አሰራርን በመዘርጋት ለክልሉ ዘላቂ ልማት እንዲውል አግዟል ብለዋል።

በክልሉ የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ ለውጡ የፋይናንስ ተቋማትን ማዘመኑ ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደር ልማት ላይ እንዲውል አስችሏል ብለዋል።


በዚህም በዞኑ የተለያዩ የበጀት ምንጮችን በአግባቡ በመጠቀም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል።

የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሀብት፣ ንብረትና ግዥ አሰራሩን ማሻሻል ተችሏል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሰላማዊት ነጋ ናቸው።

ገንዘብ በአግባቡ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የተጠናከረ ቁጥጥር እየተደረገ ነውም ብለዋል።

የሰሜን ጎጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ አቶ በላይነህ ወንድም አፈራሁ በበኩላቸው፣ የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ መቻሉ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስችሏል ብለዋል።


ከዚህ በተጨማሪም ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ለህብረተሰቡ ተአማኒነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚካሄደው መድረክ ላይም የክልሉና የዞን አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026