የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ የፋይናንስ ስርአቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል እየተሰራ ነው

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ከሚሴ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):- በአማራ ክልል የፋይናንስ ስርአቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠንና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በከሚሴ ከተማ እያካሄደ ነው።

የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን እንደገለፁት፣ የክልሉን ገቢና ወጭ በማጣጣም ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው።


ለዚህም የፋይናንስ አጠቃቀምን ዲጂታላይዝ በማድረግ በሀብት አጠቃቀምና በሌሎችም አበረታች ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።

በተለይም በመንግስት ግዥ፣ በውስጥ ኦዲት፣ በወጪ አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጡ ግልጸኝነት ያለው አሰራርን በመዘርጋት ለክልሉ ዘላቂ ልማት እንዲውል አግዟል ብለዋል።

በክልሉ የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ ለውጡ የፋይናንስ ተቋማትን ማዘመኑ ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደር ልማት ላይ እንዲውል አስችሏል ብለዋል።


በዚህም በዞኑ የተለያዩ የበጀት ምንጮችን በአግባቡ በመጠቀም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል።

የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሀብት፣ ንብረትና ግዥ አሰራሩን ማሻሻል ተችሏል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሰላማዊት ነጋ ናቸው።

ገንዘብ በአግባቡ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የተጠናከረ ቁጥጥር እየተደረገ ነውም ብለዋል።

የሰሜን ጎጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ አቶ በላይነህ ወንድም አፈራሁ በበኩላቸው፣ የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ መቻሉ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስችሏል ብለዋል።


ከዚህ በተጨማሪም ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ለህብረተሰቡ ተአማኒነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚካሄደው መድረክ ላይም የክልሉና የዞን አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026