የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎች እርካታ 98 ነጥብ 7 በመቶ ደርሷል

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2018(ኢዜአ)፦የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባለፉት 10 ወራት የዜጎችን የአገልግሎት እርካታ 98 ነጥብ 7 ማድረሱን የአገልግሎቱ ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ ገለጹ።

አገልግሎቱ በተበታተነ መልኩ የሚሰጡ አሰራሮችን በአንድ ጣሪያ ስር በማምጣት እስካሁን ከ160 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት መስጠቱንም ጠቅሰዋል።

በማዕከሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን ያገኙ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው ባጠረ ጊዜ ቀልጣፋ አገልግሎት በማግኘት ጉዳያቸውን በአግባቡ መፈጸማቸውን ተናግረዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተቋቋመው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተበታተነ መልኩ የሚሰጡ አገልገሎቶችን በአንድ ቦታ ማግኘት የሚያስችል አሰራር ነው።

የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ አንተነህ ማሞ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ተቋማት በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው በአንድ ቦታ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል አሰራር ነው።

አገልግሎቱ ከተጀመረ በ10 ወራት ውስጥ በርካታ ማዕከላትን በማቋቋም ለዜጎች ግልፅ፣ ቀልጣፋና እርካታን ያሳደገ አገልግሎት መስጠት መቻሉን ተናግረዋል።

ይህም ዜጎች በአንድ ቦታ፣ ባጠረ ጊዜና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፈ አሰራር አገልግሎት እንዲያገኙ በማስቻል ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል።

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህም በአገልግሎቱ የዜጎች እርካታ 98 ነጥብ 7 በመቶ መድረሱን ጠቁመዋል።

ወደ መሶብ ያልገቡ ተቋማት የአሠራሩ አካል እንዲሆኑና ለአገልግሎት ጥራት መሻሻል የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ለዚህም አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ክልሎችና ከተሞች አገልግሎቱን በጥራት ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶታል ነው ያሉት።

ዳይሬከተሩ አክለውም፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰጡት አቅጣጫ መሰረት የ24 ሰዓት አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት እየተሠራ ስለመሆኑም ገልጸዋል።

ንግድ ፍቃድ ለማውጣት ወደ ማዕከሉ የመጡት ተገልጋይ አደመ አየለ በሰጡት አስተያየት ቀደም ሲል የነበረው የተጓተተ ንግድ ፍቃድ የማውጣት ሂደት በመቀረፉ መደሰታቸውን ተናግረዋል።


በተቋማት መካከል የተቀናጀና የተቀላጠፈ አሠራር መዘርጋቱ እንግልትንና ምልልስን አስቀርቷል ነው ያሉት።

ለኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት የመጡት ቤተልሔም እንግዳ፥ በማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቁመዋል።


መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ እርካታን የሚፈጥር ውጤታማ አሠራር በመሆኑ ዜጎች የዚህ ዘመናዊ አሰራር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025