የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ፕሮግራሙ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለአካባቢ ውበትና ገጽታ ግንባታ ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች እየተተገበረ ያለው የልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለአካባቢ ውበትና ገጽታ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተመላከተ።

የኦሮሚያ ክልል የከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ በቀለ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም በክልሉ በ30 ከተሞች እየተተገበረ ይገኛል።

ፕሮግራሙ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ለአካባቢ ጥበቃና ለገጽታ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ተሳታፊዎቹ በአረንጓዴ ልማት፣ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና በአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤ ላይ በመሰማራት ለከተሞች ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አመልክተዋል።

ፕሮግራሙ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና በቤተሰብ ደረጃ ጥሪት ለማፍራት እያስቻለ መሆኑንም ጨምረው አብራርተዋል።

ተሳታፊዎቹ በቤተሰብ ኑሮ ማሻሻያ ዘዴዎች ላይ ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉንና ከሚያገኙት ገቢ ላይ እንዲቆጥቡ ብድር እንዲያገኙና የመሥሪያ ቦታ እንዲመቻችላቸው እየተደረገ ነው ብለዋል።

በዚህም በክልሉ በሁለት ዙር የተመለመሉ 150 ሺህ ዜጎች የሥልጠናና የፋይናንስ ድጋፍ አግኝተው በከተማ ግብርና፣ በንግድና በማምረቻው ዘርፎች ተሰማርተው ኑሯቸውን ማሻሻል መቻላቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ፕሮጀክቱ የማህበረሰቡን የሥራና የቁጠባ ባህል ማሳደጉን፣ አረጋውያንንና አቅመ ደካሞችን በቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚ ማድረጉን፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩንና መንግሥት የጀመረውን ከተረጂነት ወደ አምራችነት የመሸጋገር አቅጣጫ እያገዘ መሆኑን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ የአማራ ክልል የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም አስተባባሪ ሀሰን ኑሩዬ በበኩላቸው፤ በክልሉ በ18 ከተሞች እየተተገበረ በሚገኘው በዚህ ፕሮጀክት የበርካታ ዜጎችን ሕይወት ለመቀየርና የሥራ ባህልን ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህም ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያላቸው ዜጎች በፍትሃዊነት ተለይተው በከተማ ግብርና፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎች አዋጭ የሥራ መስኮች እንዲሰማሩ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።

በአሁኑ ወቅት በክልሉ 239 ሺህ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ያሉ ሲሆን፣ እነዚህ ዜጎች ሠርተው ከድህነት እንዲወጡ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል ሲሉም ገልጸዋል።

በሁለት ዙር ከ24 ሺህ በላይ ዜጎች በፕሮግራሙ ተመርቀው መውጣታቸውንና በተሰማሩባቸው የሥራ መስኮችም መሠረታዊ የኑሮ ለውጥ ማሳየታቸውን አብራርተዋል።

የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ድህነትና ሥራ አጥነትን በመቀነስ፣ የከተሞችን ጽዳትና ውበት በመጠበቅ እንዲሁም የተጎዱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ በኩል ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025