🔇Unmute
አዳማ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች እየተተገበረ ያለው የልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለአካባቢ ውበትና ገጽታ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተመላከተ።
የኦሮሚያ ክልል የከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ በቀለ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም በክልሉ በ30 ከተሞች እየተተገበረ ይገኛል።
ፕሮግራሙ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ለአካባቢ ጥበቃና ለገጽታ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
ተሳታፊዎቹ በአረንጓዴ ልማት፣ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና በአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤ ላይ በመሰማራት ለከተሞች ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አመልክተዋል።
ፕሮግራሙ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና በቤተሰብ ደረጃ ጥሪት ለማፍራት እያስቻለ መሆኑንም ጨምረው አብራርተዋል።
ተሳታፊዎቹ በቤተሰብ ኑሮ ማሻሻያ ዘዴዎች ላይ ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉንና ከሚያገኙት ገቢ ላይ እንዲቆጥቡ ብድር እንዲያገኙና የመሥሪያ ቦታ እንዲመቻችላቸው እየተደረገ ነው ብለዋል።
በዚህም በክልሉ በሁለት ዙር የተመለመሉ 150 ሺህ ዜጎች የሥልጠናና የፋይናንስ ድጋፍ አግኝተው በከተማ ግብርና፣ በንግድና በማምረቻው ዘርፎች ተሰማርተው ኑሯቸውን ማሻሻል መቻላቸውን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ፕሮጀክቱ የማህበረሰቡን የሥራና የቁጠባ ባህል ማሳደጉን፣ አረጋውያንንና አቅመ ደካሞችን በቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚ ማድረጉን፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩንና መንግሥት የጀመረውን ከተረጂነት ወደ አምራችነት የመሸጋገር አቅጣጫ እያገዘ መሆኑን ገልጸዋል።
በተመሳሳይ የአማራ ክልል የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም አስተባባሪ ሀሰን ኑሩዬ በበኩላቸው፤ በክልሉ በ18 ከተሞች እየተተገበረ በሚገኘው በዚህ ፕሮጀክት የበርካታ ዜጎችን ሕይወት ለመቀየርና የሥራ ባህልን ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዚህም ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያላቸው ዜጎች በፍትሃዊነት ተለይተው በከተማ ግብርና፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎች አዋጭ የሥራ መስኮች እንዲሰማሩ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።
በአሁኑ ወቅት በክልሉ 239 ሺህ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ያሉ ሲሆን፣ እነዚህ ዜጎች ሠርተው ከድህነት እንዲወጡ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል ሲሉም ገልጸዋል።
በሁለት ዙር ከ24 ሺህ በላይ ዜጎች በፕሮግራሙ ተመርቀው መውጣታቸውንና በተሰማሩባቸው የሥራ መስኮችም መሠረታዊ የኑሮ ለውጥ ማሳየታቸውን አብራርተዋል።
የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ድህነትና ሥራ አጥነትን በመቀነስ፣ የከተሞችን ጽዳትና ውበት በመጠበቅ እንዲሁም የተጎዱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ በኩል ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑ ተገልጿል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025