የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎችን ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ውጤት እያስገኘ ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎችን ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተጀመረው ሥራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡

የክልሉ የሥራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት የሰባት ወራት የሥራ አፈጻጻም ግምገማ ተካሂዷል።

በለውጡ ዓመታት በሸበሌ ዞን፣ ጎዴ እና ደገሃቡር ከተሞች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል


በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እንደገለጹት፡ ባለፉት ሰባት ወራት በሥራ ዕድል ፈጠራ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው፡፡

በበጀት ዓሙቱ ለ71 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱን ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ በእስካሁን ሂደት ለ 55 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡

የክልሉ መንግስት የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸውን ዜጎች ውጤታማ ለማድረግ ከስልጠና ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የጀመረው ሥራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ አጫጭር ስልጠናዎች ከመስጠት ባለፈ ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

በቀሪ ወራትም ለክልሉ ወጣቶች የመሸጫና የማምረቻ ቦታዎችን እንዲሁም የገንዘብ ብድር በማመቻቸት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ ነው ያስታወቁት።

የክልሉ ሥራ፣ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረፅዮን አበበ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ሥራ የተፈጠረላቸውን ዜጎች ውጤታማ ለማድረግ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡


ከተለመደው አሰራር በመውጣት ባለድርሻ አካላት የሥራ ዕድል ፈጠራን በባለቤትነት እንዲመሩ በመደረጉ የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎችን የሀብት ባለቤት በማድረግ ረገድ አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

በክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቷል ያሉት ደግሞ የቢሮው ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ ናቸው፡፡

በዚህም ወደስራ ለሚገቡ ወጣቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ስልጠናና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፣ ከ4ሺህ 400 በላይ ዜጎችም የውጭ ሃገር የሥራ ስምሪት አግኝተዋል ብለዋል።


በክልሉ ከተፈጠረው የሥራ ዕድል 60 በመቶ የሚሆነው በግብርና ዘርፍ መሆኑን የገለጹት ምክትል ቢሮ ሃላፊው፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎችና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በርካታ ወጣቶች ተሰማርተዋል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ ለነባር ኢንተርፕራይዞች የስልጠና፣ የብድር፣ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ድጋፍ ከመደረጉ በተጨማሪ የገበያ ትስስር በመፍጠር አቅማቸውን የማሳደግ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉ መዋቅሮች የተውጣጡ የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026