🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ሕዝብ ሰላምና ልማት ይገባዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ መሆኑን ጠቁመው፤ የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑንም ገልጸዋል።
የትግራይ ክልል ዕረፍት ይፈልጋል፤ ሰላም ይፈልጋል፤ ልማት ይፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል።
ክልሉ በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም እንደሚገባው ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ ደግሞ በአረጀ አስተሳሰብ ሊረጋገጥ አይችልም ብለዋል።
በእርጅናቸው ጊዜ ጦርነት የሚቀሰቅሱትን ደግሞ ተዉ ሊባሉ እና የሀገራችንን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።
መንግስት የህዝቡን ፍላጎት ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑንም ነው ጨምረው የገለጹት።
ከሰላም ፈላጊዎች ጋር፤ ከተማሩ ወጣቶች ጋር ተባብረን ለትግራይ ክልል ሰላምና ልማት እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026