🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ሕዝብ ሰላምና ልማት ይገባዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ መሆኑን ጠቁመው፤ የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑንም ገልጸዋል።
የትግራይ ክልል ዕረፍት ይፈልጋል፤ ሰላም ይፈልጋል፤ ልማት ይፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል።
ክልሉ በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም እንደሚገባው ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ ደግሞ በአረጀ አስተሳሰብ ሊረጋገጥ አይችልም ብለዋል።
በእርጅናቸው ጊዜ ጦርነት የሚቀሰቅሱትን ደግሞ ተዉ ሊባሉ እና የሀገራችንን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።
መንግስት የህዝቡን ፍላጎት ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑንም ነው ጨምረው የገለጹት።
ከሰላም ፈላጊዎች ጋር፤ ከተማሩ ወጣቶች ጋር ተባብረን ለትግራይ ክልል ሰላምና ልማት እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026