🔇Unmute
ሀዋሳ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።
በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ላደረጉ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ተካሄዷል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው።
የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ስራ አጥ ዜጎችን ወደ ስራ ለማስገባት በሚደረገው ጥረት በክልሉ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የፋይናንስና የክህሎት ስልጠና በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።
የክልሉ መንግስት ከአጋር አካላት ጋር የጀመረውን ቅንጅት በማጠናከር በዘርፉ የሚከናወነውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በበኩላቸው፤ በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ዘርፍ ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን በመተግበር ሂደት የክህሎት ልማት ላይ የተከናወኑ ተግባራት በዘርፉ ለተገኘው ውጤት ጉልህ ሚናን አበርክቷል ብለዋል።
የስራ እድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ኢንዱስትሪውን እንዲቀላቀሉ በሚደረገው ጥረት የማምረቻና መሸጫ ቦታዎችን በማዘጋጀትና የማሽነሪ ድጋፍ መደረጉንም ተናግረዋል።

የዛሬው መድረክ ዋና ዓላማም እስካሁን ለተከናወነው ተግባር ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት ቅንጅቱን የማጠናከር ስራ ለመስራት ነው ብለዋል።
በክልሉ የሚንቀሳቀሱ አጋር አካላት በተያዘው በጀት ዓመት ከ39 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስልጠና ድጋፍ ማድረጋቸውም ታውቋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026