የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።

በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ላደረጉ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ተካሄዷል።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው።

የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ስራ አጥ ዜጎችን ወደ ስራ ለማስገባት በሚደረገው ጥረት በክልሉ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የፋይናንስና የክህሎት ስልጠና በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።

የክልሉ መንግስት ከአጋር አካላት ጋር የጀመረውን ቅንጅት በማጠናከር በዘርፉ የሚከናወነውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በበኩላቸው፤ በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ዘርፍ ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።


በተለይም ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን በመተግበር ሂደት የክህሎት ልማት ላይ የተከናወኑ ተግባራት በዘርፉ ለተገኘው ውጤት ጉልህ ሚናን አበርክቷል ብለዋል።

የስራ እድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ኢንዱስትሪውን እንዲቀላቀሉ በሚደረገው ጥረት የማምረቻና መሸጫ ቦታዎችን በማዘጋጀትና የማሽነሪ ድጋፍ መደረጉንም ተናግረዋል።


የዛሬው መድረክ ዋና ዓላማም እስካሁን ለተከናወነው ተግባር ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት ቅንጅቱን የማጠናከር ስራ ለመስራት ነው ብለዋል።

በክልሉ የሚንቀሳቀሱ አጋር አካላት በተያዘው በጀት ዓመት ከ39 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስልጠና ድጋፍ ማድረጋቸውም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026