🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝ ለማድረግ 4ኛው ምዕራፍ የዲስትሪቢዩሽን መስመር መልሶ ግንባታና ዐቅም ማሳደግ ፕሮጀክት እየተከናወነ ነው።
ሥራው እየተከናወነ የሚገኘው በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት ሥራው 703 ኪሎ ሜትር የዲስትሪቢዩሽን ኔትዎርክ መልሶ ግንባታና ዐቅም ማሳደግን ያካተተ መሆኑን አመላክተዋል።
በተጨማሪም 2 ሺህ አዲስ የተለያየ ዐቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች ተከላና 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮችን ዐቅም የማሳደግ ሥራ የሚከናወንበት መሆኑን ጠቁመዋል።

በፕሮጀክቱ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወጪ የሚሆኑ 56 ማሰራጫ መስመሮችን መልሶ የመገንባትና የማሻሻል እንዲሁም ከተፈቀደው የኃይል አጠቃቀም በላይ ሲሆን መቆጣጠር የሚያስችሉ 62 የሎድ ብሬክ ስዊች ገጠማ ይከናወናል ብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የፊዚካል ሥራ አፈፃፀም 36 ነጥብ 74 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ 2 ሺህ 857 የኮንክሪት ምሰሶዎች ተከላ ሥራም መከናወኑን አስታውቀዋል።

ሥራው ሲጠናቀቅ በአዲስ አበባና በሸገር ከተሞች በዓመት በ100 ኪ.ሜ የመካከለኛ የኃይል ማሰራጫ መስመር ላይ የሚከሰተውን የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽን በ27 በመቶ ለመቀነስ ያስችላል ነው ያሉት።
የትራንስፎርመር መቃጠልንም ወደ 2 በመቶ መቀነስ እንደሚያስችል አመላክተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026