🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝ ለማድረግ 4ኛው ምዕራፍ የዲስትሪቢዩሽን መስመር መልሶ ግንባታና ዐቅም ማሳደግ ፕሮጀክት እየተከናወነ ነው።
ሥራው እየተከናወነ የሚገኘው በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት ሥራው 703 ኪሎ ሜትር የዲስትሪቢዩሽን ኔትዎርክ መልሶ ግንባታና ዐቅም ማሳደግን ያካተተ መሆኑን አመላክተዋል።
በተጨማሪም 2 ሺህ አዲስ የተለያየ ዐቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች ተከላና 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮችን ዐቅም የማሳደግ ሥራ የሚከናወንበት መሆኑን ጠቁመዋል።

በፕሮጀክቱ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወጪ የሚሆኑ 56 ማሰራጫ መስመሮችን መልሶ የመገንባትና የማሻሻል እንዲሁም ከተፈቀደው የኃይል አጠቃቀም በላይ ሲሆን መቆጣጠር የሚያስችሉ 62 የሎድ ብሬክ ስዊች ገጠማ ይከናወናል ብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የፊዚካል ሥራ አፈፃፀም 36 ነጥብ 74 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ 2 ሺህ 857 የኮንክሪት ምሰሶዎች ተከላ ሥራም መከናወኑን አስታውቀዋል።

ሥራው ሲጠናቀቅ በአዲስ አበባና በሸገር ከተሞች በዓመት በ100 ኪ.ሜ የመካከለኛ የኃይል ማሰራጫ መስመር ላይ የሚከሰተውን የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽን በ27 በመቶ ለመቀነስ ያስችላል ነው ያሉት።
የትራንስፎርመር መቃጠልንም ወደ 2 በመቶ መቀነስ እንደሚያስችል አመላክተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026