🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝ ለማድረግ 4ኛው ምዕራፍ የዲስትሪቢዩሽን መስመር መልሶ ግንባታና ዐቅም ማሳደግ ፕሮጀክት እየተከናወነ ነው።
ሥራው እየተከናወነ የሚገኘው በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት ሥራው 703 ኪሎ ሜትር የዲስትሪቢዩሽን ኔትዎርክ መልሶ ግንባታና ዐቅም ማሳደግን ያካተተ መሆኑን አመላክተዋል።
በተጨማሪም 2 ሺህ አዲስ የተለያየ ዐቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች ተከላና 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮችን ዐቅም የማሳደግ ሥራ የሚከናወንበት መሆኑን ጠቁመዋል።

በፕሮጀክቱ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወጪ የሚሆኑ 56 ማሰራጫ መስመሮችን መልሶ የመገንባትና የማሻሻል እንዲሁም ከተፈቀደው የኃይል አጠቃቀም በላይ ሲሆን መቆጣጠር የሚያስችሉ 62 የሎድ ብሬክ ስዊች ገጠማ ይከናወናል ብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የፊዚካል ሥራ አፈፃፀም 36 ነጥብ 74 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ 2 ሺህ 857 የኮንክሪት ምሰሶዎች ተከላ ሥራም መከናወኑን አስታውቀዋል።

ሥራው ሲጠናቀቅ በአዲስ አበባና በሸገር ከተሞች በዓመት በ100 ኪ.ሜ የመካከለኛ የኃይል ማሰራጫ መስመር ላይ የሚከሰተውን የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽን በ27 በመቶ ለመቀነስ ያስችላል ነው ያሉት።
የትራንስፎርመር መቃጠልንም ወደ 2 በመቶ መቀነስ እንደሚያስችል አመላክተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025