የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በግብርናው ዘርፍ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።

ኢንስቲትዩቱ በወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዝርያቸው የተሻሻሉ ጊደሮችና ኮርማዎችን ለሞዴል አርሶ አደሮችና በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት የማስተላለፍ እና የመስክ ምልከታ መርሃ ግብር አካሂዷል።

በወቅቱም የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ድሪባ ገለቴ(ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ በሀገሪቱ በ23 የምርምር እና በ712 የአገልግሎት ማዕከላት አዳዲስ የምርምር ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።


በሀገሪቱ አሁን ላይ ከ271 በላይ የምርምር ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባለፈ የሀገሪቱን እድገት ማፋጠን የሚያስችሉ በሳይንሳዊ ምርምር የተደገፉ ዘርፈ-ብዙ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ይህም ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል እና የእንስሳት እና ዓሳ ሃብት ዘርፍ ኃላፊ ኢያሱ ተረፈ በግብርና ምርምር የተገኘው ስኬትና ማንሰራራት ቀጣይነት እንዲኖረው የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ባለፈው ዓመት በክልሉ የወተት ምርታማነት 675 ሚሊየን ሊትር ላይ መድረሱን ጠቁመው በዘንድሮ ዓመት 744 ሚሊየን ሊትር ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ኢንስቲትዩቱ በሚያከናውናቸው የምርምር ስራዎች በዞኑ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የገለፁት ደግሞ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ ናቸው።


የለውጡ መንግስት ለግብርና ልማት በሰጠው ትኩረት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተግባራዊ መደረጉ የእንስሳት ልማቱን በግብዓትና በአዳዲስ አሰራር ለማገዝ አስችሏል ብለዋል።

የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ቤተል ነክር በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚያስችሉ የተለያዩ የግብርና ምርምር ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰዋል።


ለዓመታት የምርምርና ብዜት ሥራ ሲከናወንባቸው የነበሩ የተሻሻሉ የኮርማ፣ የጊደርና የዶሮ ዝርያዎችን ለሞዴል አርሶ አደሮች እና በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት እንዲሰጡ መደረጉንም ተናገረዋል።

የሶዶ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር አድማሱ ግዛው፤ ከእርሻ ሥራቸው ጎን ለጎን ዝርያቸው የተሻሻሉ የወተት ላሞቹን በማርባት ከሚያገኙት ምርት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ገቢያቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።


በምርምር ማእከሉ የተሰጧቸው ዝርያቸው የተሻሻሉ ዶሮዎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያሳድግላቸው የገለፁት ደግሞ በአበሽጌ ወረዳ የጣጤሳ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ መውደድ ሰርጉ ናቸው።

በወልቂጤ ከተማ ዝርያቸው የተሻሻሉ ከብቶችን በማርባት በቀን 60 ሊትር ወተት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ያነሱት ደሳለኝ ዘበርጋ(ዶ/ር) ናቸው።


በዘንድሮ ዓመትም ከምርምር ማእከሉ ዝርያቸው የተሻሻሉ ጊደሮችን ማግኘታቸውን ነው የገለጹት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026