የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በግብርናው ዘርፍ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።

ኢንስቲትዩቱ በወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዝርያቸው የተሻሻሉ ጊደሮችና ኮርማዎችን ለሞዴል አርሶ አደሮችና በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት የማስተላለፍ እና የመስክ ምልከታ መርሃ ግብር አካሂዷል።

በወቅቱም የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ድሪባ ገለቴ(ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ በሀገሪቱ በ23 የምርምር እና በ712 የአገልግሎት ማዕከላት አዳዲስ የምርምር ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።


በሀገሪቱ አሁን ላይ ከ271 በላይ የምርምር ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባለፈ የሀገሪቱን እድገት ማፋጠን የሚያስችሉ በሳይንሳዊ ምርምር የተደገፉ ዘርፈ-ብዙ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ይህም ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል እና የእንስሳት እና ዓሳ ሃብት ዘርፍ ኃላፊ ኢያሱ ተረፈ በግብርና ምርምር የተገኘው ስኬትና ማንሰራራት ቀጣይነት እንዲኖረው የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ባለፈው ዓመት በክልሉ የወተት ምርታማነት 675 ሚሊየን ሊትር ላይ መድረሱን ጠቁመው በዘንድሮ ዓመት 744 ሚሊየን ሊትር ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ኢንስቲትዩቱ በሚያከናውናቸው የምርምር ስራዎች በዞኑ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የገለፁት ደግሞ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ ናቸው።


የለውጡ መንግስት ለግብርና ልማት በሰጠው ትኩረት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተግባራዊ መደረጉ የእንስሳት ልማቱን በግብዓትና በአዳዲስ አሰራር ለማገዝ አስችሏል ብለዋል።

የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ቤተል ነክር በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚያስችሉ የተለያዩ የግብርና ምርምር ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰዋል።


ለዓመታት የምርምርና ብዜት ሥራ ሲከናወንባቸው የነበሩ የተሻሻሉ የኮርማ፣ የጊደርና የዶሮ ዝርያዎችን ለሞዴል አርሶ አደሮች እና በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት እንዲሰጡ መደረጉንም ተናገረዋል።

የሶዶ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር አድማሱ ግዛው፤ ከእርሻ ሥራቸው ጎን ለጎን ዝርያቸው የተሻሻሉ የወተት ላሞቹን በማርባት ከሚያገኙት ምርት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ገቢያቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።


በምርምር ማእከሉ የተሰጧቸው ዝርያቸው የተሻሻሉ ዶሮዎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያሳድግላቸው የገለፁት ደግሞ በአበሽጌ ወረዳ የጣጤሳ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ መውደድ ሰርጉ ናቸው።

በወልቂጤ ከተማ ዝርያቸው የተሻሻሉ ከብቶችን በማርባት በቀን 60 ሊትር ወተት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ያነሱት ደሳለኝ ዘበርጋ(ዶ/ር) ናቸው።


በዘንድሮ ዓመትም ከምርምር ማእከሉ ዝርያቸው የተሻሻሉ ጊደሮችን ማግኘታቸውን ነው የገለጹት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026