የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምዕራብ ወለጋ ዞን የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጊምቢ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን ተግባራዊ የተደረጉ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ መምጣታቸውን የዞኑ አስተዳዳር ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ ለኢዜአ እንዳሉት በዞኑ በግብርና ዘርፍ ተግባራዊ የተደረጉ ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ናቸው።

በዞኑ ከሰላም ማሰፈን ሥራ ጎን ለጎን የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰጠው ትኩረት በተለይ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ውጤታማ ሥራዎች እንደተከናወኑ ገልጸዋል።

በመርሀግብሩ ተጠቃሚነት ለማሳደግም ዘንድሮ ከ116 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሩ ለማሰራጨት ታቅዶ እስካሁን ድረስ 99 ሺህ 375 የንብ ቀፎ ተሰራጭቷል ብለዋል።

በንብ ማነብ ሥራው 15 ሺህ አርሶ አደሮች መሰማራታቸውንና በዓመቱ መጨረሻም 12 ሺህ ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን አቶ ተሊላ ጠቁመዋል።

እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለጻ፣ ከንብ ማነብ ሥራ በተጨማሪ የወተት ላሞችን ዝርያ ለማሻሻል እና ለሥጋና እንቁላል ጣይ ዶሮዎች ስርጭት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

የሰብል ልማት ምርታማነትን ለማሳደግም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በግብርና ቴክኖሎጂ የመደገፍና የማስፋፋት ሥራ ተከናውኗል።

በዞኑ ያለውን የመስኖ አቅም በማሳደግ አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት የማላቀቅና የሜካናይዜሽን እርሻ ልማትን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ተሊላ አመልክተዋል።

በዘንድሮ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዞኑ ከ199 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ጠቁመው፣ ከዚህም 7 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።

የስንዴ ልማቱ በኩታገጥም እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት አቶ ተሊላ፣ ይህም አርሶ አደሮች ለሰብላቸው በጋራ ክትትልና እንክብካቤ በማድረግ የተሻለ ምርት እንዲገኝ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

ከስንዴ ልማቱ በተጨማሪ ከ20 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ገበያ ተኮር የሆኑ አትክልቶች እየለሙ መሆኑንም አስረድተዋል።

ከአትክልት ልማቱም 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው አቶ ተሊላ የገለጹት።

በመስኖ ልማቱ ከ134 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸው፣ በዞኑ የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትናና ሉአላዊነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ በጊ ወረዳ ነዋሪ ሱሌማን ሞሐመድ እና ኑሩ ከላሜ በማህበር ተደራጅተው በሁለት ሄክታር መሬት ላይ በሚያከናውኑት ጥምር ግብርና ተጠቃሚ ሆነዋል።

በመስኖ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ አትክልቶች በማልማት ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025