የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምዕራብ ወለጋ ዞን የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጊምቢ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን ተግባራዊ የተደረጉ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ መምጣታቸውን የዞኑ አስተዳዳር ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ ለኢዜአ እንዳሉት በዞኑ በግብርና ዘርፍ ተግባራዊ የተደረጉ ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ናቸው።

በዞኑ ከሰላም ማሰፈን ሥራ ጎን ለጎን የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰጠው ትኩረት በተለይ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ውጤታማ ሥራዎች እንደተከናወኑ ገልጸዋል።

በመርሀግብሩ ተጠቃሚነት ለማሳደግም ዘንድሮ ከ116 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሩ ለማሰራጨት ታቅዶ እስካሁን ድረስ 99 ሺህ 375 የንብ ቀፎ ተሰራጭቷል ብለዋል።

በንብ ማነብ ሥራው 15 ሺህ አርሶ አደሮች መሰማራታቸውንና በዓመቱ መጨረሻም 12 ሺህ ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን አቶ ተሊላ ጠቁመዋል።

እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለጻ፣ ከንብ ማነብ ሥራ በተጨማሪ የወተት ላሞችን ዝርያ ለማሻሻል እና ለሥጋና እንቁላል ጣይ ዶሮዎች ስርጭት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

የሰብል ልማት ምርታማነትን ለማሳደግም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በግብርና ቴክኖሎጂ የመደገፍና የማስፋፋት ሥራ ተከናውኗል።

በዞኑ ያለውን የመስኖ አቅም በማሳደግ አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት የማላቀቅና የሜካናይዜሽን እርሻ ልማትን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ተሊላ አመልክተዋል።

በዘንድሮ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዞኑ ከ199 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ጠቁመው፣ ከዚህም 7 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።

የስንዴ ልማቱ በኩታገጥም እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት አቶ ተሊላ፣ ይህም አርሶ አደሮች ለሰብላቸው በጋራ ክትትልና እንክብካቤ በማድረግ የተሻለ ምርት እንዲገኝ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

ከስንዴ ልማቱ በተጨማሪ ከ20 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ገበያ ተኮር የሆኑ አትክልቶች እየለሙ መሆኑንም አስረድተዋል።

ከአትክልት ልማቱም 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው አቶ ተሊላ የገለጹት።

በመስኖ ልማቱ ከ134 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸው፣ በዞኑ የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትናና ሉአላዊነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ በጊ ወረዳ ነዋሪ ሱሌማን ሞሐመድ እና ኑሩ ከላሜ በማህበር ተደራጅተው በሁለት ሄክታር መሬት ላይ በሚያከናውኑት ጥምር ግብርና ተጠቃሚ ሆነዋል።

በመስኖ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ አትክልቶች በማልማት ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026