የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ጋር የተጀመረው ቅንጅታዊ ስራ ይጠናከራል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ዓመታት የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ጋር የተጀመረው ቅንጅታዊ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን "በተቀናጀና ቀጣይነት ባለው የድጋፍ ማዕቀፍ አምራቿንና ምርታማዋን ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እንፈጥራለን" በሚል መሪ ሃሳብ ክልል አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም በወላይታ ሶዶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።


በፎረሙ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድሩ በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በመቅረፍ አልሚ ባለሃብቶችን ማበረታታትና መደገፍ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ጋር በቅንጅት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

ክልሉ ያለውን ዕምቅ የኢንቨስትመንት አቅም በመጠቀም የሰላም፣ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ በተጀመረው ጥረት የግሉ ባለሀብት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

በመሆኑም ባሉን አቅሞችና ዕድሎች ዙሪያ በመወያየት ክልሉ ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም ማግኘት እንዲችል የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልጸዋል።


የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አፀደ አይዛ በበኩላቸው በክልሉ 82 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 1ሺህ 826 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ ገብተው በርካቶችን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆናቸውን አንስተዋል።

ክልሉ ከተመሰረተ በኃላ ከ49 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 536 የኢቨስትመንት ፕሮጀክቶች በኢንቨስትመንት ቦርድ ፈቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡

ፕሮጀክቶቹ ለስራ እድል ፈጠራ፣ ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ አገልግሎት መስፋፋት ጉልህ ሚና እያበረከቱ መሆኑን ገልጸው በክልሉ ያለውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው ማልማት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች ተገቢው ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025