የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ጋር የተጀመረው ቅንጅታዊ ስራ ይጠናከራል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ዓመታት የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ጋር የተጀመረው ቅንጅታዊ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን "በተቀናጀና ቀጣይነት ባለው የድጋፍ ማዕቀፍ አምራቿንና ምርታማዋን ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እንፈጥራለን" በሚል መሪ ሃሳብ ክልል አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም በወላይታ ሶዶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።


በፎረሙ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድሩ በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በመቅረፍ አልሚ ባለሃብቶችን ማበረታታትና መደገፍ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ጋር በቅንጅት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

ክልሉ ያለውን ዕምቅ የኢንቨስትመንት አቅም በመጠቀም የሰላም፣ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ በተጀመረው ጥረት የግሉ ባለሀብት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

በመሆኑም ባሉን አቅሞችና ዕድሎች ዙሪያ በመወያየት ክልሉ ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም ማግኘት እንዲችል የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልጸዋል።


የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አፀደ አይዛ በበኩላቸው በክልሉ 82 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 1ሺህ 826 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ ገብተው በርካቶችን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆናቸውን አንስተዋል።

ክልሉ ከተመሰረተ በኃላ ከ49 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 536 የኢቨስትመንት ፕሮጀክቶች በኢንቨስትመንት ቦርድ ፈቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡

ፕሮጀክቶቹ ለስራ እድል ፈጠራ፣ ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ አገልግሎት መስፋፋት ጉልህ ሚና እያበረከቱ መሆኑን ገልጸው በክልሉ ያለውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው ማልማት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች ተገቢው ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026