🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከንግድ አበዳሪዎች ጋር የምታደርገውን ድርድር ለማጠናቀቅ በምታደርገው ጥረት የቻይና ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ጥሪ አቀረቡ።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ እና ከቻይና ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ (China Exim Bank) የልዑካን ቡድን ጋር በጋራ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
ውይይቱ በዋናነት ትኩረቱን ያደረገው በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ ሊኖሩ በሚችሉ የገንዘብ ድጋፍ አማራጮች ዙሪያ ነው።
በተጨማሪም፣ በኢትዮጵያ የቡድን 20 (G20) የጋራ ማዕቀፍ የዕዳ ሽግሽግ (debt restructuring) ሂደት አስመልክቶ በሁለቱ ወገኖች መካከል ምክክር ተደርጓል።
ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ ቻይና የአበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ሰብሳቢ በመሆን ላሳየችው አመራርና በዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ ወቅት ላደረገችው ገንቢ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ሂደቱ አሁን ላይ በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የሚገኝ በመሆኑ፣ የተጀመረውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል።
አያይዘውም፣ ኢትዮጵያ ከንግድ አበዳሪዎች(commercial creditors) ጋር የምታደርገውን ድርድር በማጠናቀቅ በኩል የቻይና ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመላክቷል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025