🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከንግድ አበዳሪዎች ጋር የምታደርገውን ድርድር ለማጠናቀቅ በምታደርገው ጥረት የቻይና ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ጥሪ አቀረቡ።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ እና ከቻይና ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ (China Exim Bank) የልዑካን ቡድን ጋር በጋራ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
ውይይቱ በዋናነት ትኩረቱን ያደረገው በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ ሊኖሩ በሚችሉ የገንዘብ ድጋፍ አማራጮች ዙሪያ ነው።
በተጨማሪም፣ በኢትዮጵያ የቡድን 20 (G20) የጋራ ማዕቀፍ የዕዳ ሽግሽግ (debt restructuring) ሂደት አስመልክቶ በሁለቱ ወገኖች መካከል ምክክር ተደርጓል።
ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ ቻይና የአበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ሰብሳቢ በመሆን ላሳየችው አመራርና በዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ ወቅት ላደረገችው ገንቢ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ሂደቱ አሁን ላይ በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የሚገኝ በመሆኑ፣ የተጀመረውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል።
አያይዘውም፣ ኢትዮጵያ ከንግድ አበዳሪዎች(commercial creditors) ጋር የምታደርገውን ድርድር በማጠናቀቅ በኩል የቻይና ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመላክቷል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026