🔇Unmute
ሰቆጣ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የቡና ልማትን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ ነው።
በአሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ የመስኖ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን መሪ ደሳለኝ አዳነ እንዳሉት፤ እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ2 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በ36 ሔክታር ላይ የቡና ልማት ተከናውኗል።
በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብርም በ11 ሔክታር ላይ በኩታ ገጠም ለማልማት የሚያስችል 16 ሺህ 854 የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን ለኢዜአ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ለቡና ልማት ተስማሚ የዓየር ንብረትና ሥነ-ምኅዳር ያላቸውን አካባቢዎች የመለየትና አርሶ አደሮቹን የማዘጋጀት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አመላክተዋል።
በዚህም 1 ሺህ 324 አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ ጠቁመው፤ የቡና ልማቱም በኩታ ገጠም የእርሻ ሥነ-ዘዴ ይከናወናል ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026