🔇Unmute
ሰቆጣ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የቡና ልማትን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ ነው።
በአሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ የመስኖ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን መሪ ደሳለኝ አዳነ እንዳሉት፤ እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ2 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በ36 ሔክታር ላይ የቡና ልማት ተከናውኗል።
በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብርም በ11 ሔክታር ላይ በኩታ ገጠም ለማልማት የሚያስችል 16 ሺህ 854 የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን ለኢዜአ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ለቡና ልማት ተስማሚ የዓየር ንብረትና ሥነ-ምኅዳር ያላቸውን አካባቢዎች የመለየትና አርሶ አደሮቹን የማዘጋጀት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አመላክተዋል።
በዚህም 1 ሺህ 324 አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ ጠቁመው፤ የቡና ልማቱም በኩታ ገጠም የእርሻ ሥነ-ዘዴ ይከናወናል ብለዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026