የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የልማት ጥያቄያችን ምላሽ እያገኘ በመሆኑ ተደስተናል−የደቡብ ኦሞ ዞን ነዋሪዎች

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦የብዙ ዓመታት የልማት ጥያቄያቸው ምላሽ እያገኘ በመምጣቱ መደሰታቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ የሀና ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

በማጎ ብሔራዊ ፓርክ እና በኦሞ ኩራዝ ስኳር ፕሮጀክት አካባቢ የምትገኘው የሀና ከተማ ከአዲስ አበባ ወደ 900 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።

ድሬዳዋን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል--ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ

የሀና ከተማ በዙሪያዋ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 1 እና 2 ፕሮጀክት እንዲሁም ሰፋፊ የግል ኢንቨስትመንቶች የሚገኝባት ስትሆን ሰሊጥ እና ማሾም በአካባቢው በስፋት ይመረታል፡፡

ከተማዋ ዕድሜ ጠገብ ብትሆንም ዕድገቷ የዕድሜዋን ያህል አለመሆኑ ግን በነዋሪዎቿ ዘንድ ቅሬታን ሲፈጥር ቆይቷል።

የንጹህ መጠጥ ውሃ ፣ የኤሌክትሪክና እና ደረጃውን የጠበቀ የአስፋልት መንገድ በነዋሪዎች ዘንድ ለዘመናት ሲነሱ የነበሩ የልማት ጥያቄዎች ናቸው።

መንግስት ጥያቄዎችን ሰምቶ ያስጀመረው የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ በጥሩ ሂደት ላይ መገኘቱ ተስፋቸውን እንዳለመለመው ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ አመለወርቅ ካሱ፤ የከተማዋ ልማት አለመፋጠኑ ለዘመናት ቁጭት ፈጥሮባቸው እንደነበር አስታውሰዋል።


የለውጡ መንግስት ለልማት ጥያቄያቸው ትኩረት ሰጥቶ ከተማዋን ከሌሎች ከተሞች እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ ደረጃውን የጠበቀ የአስፋልት መንገድ በማስጀመሩ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ሌላው የሀና ከተማ ነዋሪና በጡረታ የሚተዳደሩት ሜጀር ጄኔራል አለሙ አየነ በበኩላቸው፤ ከተማዋ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ እንደሆነች ጠቁመው፣ ልማቷን ማፋጠን ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።


ከህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች አንዱ ምላሽ በማግኘቱ ተስፋቸው መደሰታቸውን ገልፀው፣ በቀጣይም የንፁህ መጠጥ ውሃና የኤሌክትሪክ ጥያቄያቸው ምላሽ እንደሚያገኝ ያላቸውን እምነት ተናግረዋል።

በከተማዋ ቀደም ሲል የነበረው የሰላም እጦት ለእድገቷ ችግር ፈጥሮ እንደነበር የገለጸው ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ ወጣት ኤርስ ባባይቴ ነው።


የሀና ከተማ እንደ ሌሎች ከተሞች የልማት ተጠቃሚ እንድትሆን የአካባቢው ወጣቶች ህዝብን ለልማት በማስተባበር የበኩላቸውን እየተወጡና ከወረዳው አመራሮች ጋርም በቅርበት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የሀና ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ደበበ በበኩላቸው እንዳሉት፣ ማዘጋጃ ቤቱ የከተማዋን ነዋሪዎች የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት እየሰራ ይገኛል።


በከተማው የኮሪደር ልማት አካል የሆነው 3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የአስፋልት መንገድ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑንና በአሁኑ ወቅትም ግንባታው 80 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል።

የአስፋልት መንገዱን በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ፀጋዬ፣ በቀጣይም የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛ መንገድ፣ አደባባይ የማስዋብና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ለማከናወን መታቀዱን ገልጸዋል።

የሀና ከተማን ለቱሪዝምና ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ተመራጭና ውብ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም የገለጹት ደግሞ የሣላማጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ህጉ ቅጣቴ ናቸው።


የህዝብን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ለማሟላት በመንግስት ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው፣ በከተማዋ የተጀመረው መሰረተ ልማትን የማሟላት ሥራ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025