የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የግብርና ምርታማነትን ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፋይናንስ አቅርቦት ምኅዳር እየተፈጠረ ነው

Mar 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፋይናንስ አቅርቦት ምኅዳር እየተፈጠረ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።

የግብርና ሚኒስቴር ከክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የቢሮ ኃላፊዎችና በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሰማሩ ባለኃብቶች ጋር በግብርና ኢንቨስትመንት አፈጻጸም ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሂዷል።


በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፤ የኢትዮጵያ ዘመናዊ የግብርና ምርታማነት በማስቀጠል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የግል ባለሃብቱ ሚና ወሳኝ ነው ብለዋል።

አሁን ላይ በኢትዮጵያ 21 ሚሊየን ሔክታር የእርሻ መሬት እየለማ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በቀጣይም መታረስ የሚችል 38 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለማልማት የአነስተኛ ባለይዞታ አርሶ አደሮችንና ሰፋፊ የእርሻ ኢንቨስትመንት አቅምን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለዚህም አዳዲስ የፖሊሲ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶችን የእርሻ ኢንቨስትመንት የሚያበረታታ ምኅዳር እየተፈጠረ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የእርሻ ኢንቨስትመንት የፋይናንስ ማነቆዎችን መፍትሔ ለመስጠት የግብርና ባንክ ማቋቋም የሚያስችል የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ መደረሱን አስታውቀዋል።

በቅርቡም በሙከራ ትግበራ ደረጃ በተለያዩ ወረዳዎች የአርሶ አደሮች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት በይፋ እንደሚጀመር አንስተዋል።

በተጨማሪም የልማት አጋሮችና የፋይናንስ ተቋማት ለኢትዮጵያ የግብርና ሥርዓት መሻሻል የገንዘብ ብድር የሚያቀርቡበትን ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፋይናንስ አቅርቦት ምኅዳር እየተፈጠረ እደሚገኝ አብራርተዋል።


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የእርሻ ኢንቨስትመንት አልሚ ባለሃብቶች የሚቀርብላቸውን የገንዘብ ብድር ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል።

ከተሳታፊዎች መካከል አቶ በለው ወንድም የእርሻ ኢንቨስትመንትን ለማሻሻል የሚደረገው የፋይናንስ አቅርቦት ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ ጠቃሜታ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026