የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የግብርና ምርታማነትን ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፋይናንስ አቅርቦት ምኅዳር እየተፈጠረ ነው

Mar 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፋይናንስ አቅርቦት ምኅዳር እየተፈጠረ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።

የግብርና ሚኒስቴር ከክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የቢሮ ኃላፊዎችና በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሰማሩ ባለኃብቶች ጋር በግብርና ኢንቨስትመንት አፈጻጸም ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሂዷል።


በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፤ የኢትዮጵያ ዘመናዊ የግብርና ምርታማነት በማስቀጠል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የግል ባለሃብቱ ሚና ወሳኝ ነው ብለዋል።

አሁን ላይ በኢትዮጵያ 21 ሚሊየን ሔክታር የእርሻ መሬት እየለማ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በቀጣይም መታረስ የሚችል 38 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለማልማት የአነስተኛ ባለይዞታ አርሶ አደሮችንና ሰፋፊ የእርሻ ኢንቨስትመንት አቅምን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለዚህም አዳዲስ የፖሊሲ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶችን የእርሻ ኢንቨስትመንት የሚያበረታታ ምኅዳር እየተፈጠረ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የእርሻ ኢንቨስትመንት የፋይናንስ ማነቆዎችን መፍትሔ ለመስጠት የግብርና ባንክ ማቋቋም የሚያስችል የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ መደረሱን አስታውቀዋል።

በቅርቡም በሙከራ ትግበራ ደረጃ በተለያዩ ወረዳዎች የአርሶ አደሮች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት በይፋ እንደሚጀመር አንስተዋል።

በተጨማሪም የልማት አጋሮችና የፋይናንስ ተቋማት ለኢትዮጵያ የግብርና ሥርዓት መሻሻል የገንዘብ ብድር የሚያቀርቡበትን ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፋይናንስ አቅርቦት ምኅዳር እየተፈጠረ እደሚገኝ አብራርተዋል።


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የእርሻ ኢንቨስትመንት አልሚ ባለሃብቶች የሚቀርብላቸውን የገንዘብ ብድር ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል።

ከተሳታፊዎች መካከል አቶ በለው ወንድም የእርሻ ኢንቨስትመንትን ለማሻሻል የሚደረገው የፋይናንስ አቅርቦት ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ ጠቃሜታ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026