🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ) ፦ በሀረሪ ክልል መንግስት ከወሰነው የነዳጅ ታሪፍ በላይ እንዲሁም ከግብይት ሰንሰለት ውጪ ሲሸጡ በተገኙ ሁለት ነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ አስታውቋል።
የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ እንደገለፁት እርምጃ የተወሰደባቸው ነዳጅ ማደያዎች መንግሥት ከወሰነው ታሪፍ በላይ በመሸጥ እንዲሁም ከመደበኛው ገበያ ውጭ በስውር ለጥቁር ገበያ ሲሸጡ በመገኘታቸው ነው።

ነዳጅ ማደያዎቹ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ተደጋጋሚ የፅሁፍና የቃል ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ቢሆንም ከድርጊታቸው ሊታቀቡ እንዳልቻሉም ኃላፊው አስረድተዋል።
በዚህም ማደያዎቹ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ምንም አይነት የነዳጅ ምርት እንዳይሸጡ ተደርገዋል ብለዋል።
በነዳጅ ግብይት ላይ የሚደረገው ክትትልና ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊው ጠቁመዋል ።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026