🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ በኢነርጂ ዘርፍ የሀገሪቱ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ወደ ተግባር መግባቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር አብዱልፈታህ ራቢ ገለጹ።
ኢነርጂ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እድገት መሰረት ሲሆን በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት የኢነርጂ አቅርቦት ከኢንዱስትሪ መስፋፋት፣ ከግብርና ዘመናዊነትና ከዜጎች የኑሮ ደረጃ መሻሻል ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አለው፡፡
በመሆኑም በኢነርጂ ዘርፍ እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ያለው ቁርኝት ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገትና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ወሳኝ ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን ተቋማቱ የሀገርን የኢነርጂ ዘርፍ በማዘመን በኩል የማይተካ ሚና አላቸው፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር አብዱልፈታህ ራቢ ሀገራዊ ተልዕኮውን እውን ለማድረግ በዘርፉ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራትና ምርምሮችን ለማካሄድ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በተያዘው የትምህርት ዘመን በፔትሮሊየም ኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፍ ማስተማር መጀመሩን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ከኢነርጂ ዘርፍ ጋር የተያያዙ 27 የሁለተኛ ድግሪ እና 36 የመጀመሪያ ድግሪ ፕሮግራሞች ተከፍተው ስራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
በዚህም በኢነርጂ ዘርፍ የሀገሪቱ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤታማነት ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ የትምህርት ጥራቱን ለማሳደግና ዓለምአቀፍ ልምዶችን ለመቅሰም በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ካላቸው የቻይና ዩኒቨርሲቲዎች እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጸዋል።
ለሀገሪቱ የኢነርጂ ኢንዱስትሪ የሚመጥኑ፣ በዕውቀትና በክህሎት የበለጸጉ ባለሙያዎችን በማፍራት በኩል ዩኒቨርሲቲው ግንባር ቀደም ሚና እንደሚጫወት ፕሬዚዳንቱ አረጋግጠዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026