🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ በኢነርጂ ዘርፍ የሀገሪቱ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ወደ ተግባር መግባቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር አብዱልፈታህ ራቢ ገለጹ።
ኢነርጂ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እድገት መሰረት ሲሆን በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት የኢነርጂ አቅርቦት ከኢንዱስትሪ መስፋፋት፣ ከግብርና ዘመናዊነትና ከዜጎች የኑሮ ደረጃ መሻሻል ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አለው፡፡
በመሆኑም በኢነርጂ ዘርፍ እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ያለው ቁርኝት ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገትና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ወሳኝ ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን ተቋማቱ የሀገርን የኢነርጂ ዘርፍ በማዘመን በኩል የማይተካ ሚና አላቸው፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር አብዱልፈታህ ራቢ ሀገራዊ ተልዕኮውን እውን ለማድረግ በዘርፉ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራትና ምርምሮችን ለማካሄድ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በተያዘው የትምህርት ዘመን በፔትሮሊየም ኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፍ ማስተማር መጀመሩን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ከኢነርጂ ዘርፍ ጋር የተያያዙ 27 የሁለተኛ ድግሪ እና 36 የመጀመሪያ ድግሪ ፕሮግራሞች ተከፍተው ስራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
በዚህም በኢነርጂ ዘርፍ የሀገሪቱ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤታማነት ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ የትምህርት ጥራቱን ለማሳደግና ዓለምአቀፍ ልምዶችን ለመቅሰም በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ካላቸው የቻይና ዩኒቨርሲቲዎች እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጸዋል።
ለሀገሪቱ የኢነርጂ ኢንዱስትሪ የሚመጥኑ፣ በዕውቀትና በክህሎት የበለጸጉ ባለሙያዎችን በማፍራት በኩል ዩኒቨርሲቲው ግንባር ቀደም ሚና እንደሚጫወት ፕሬዚዳንቱ አረጋግጠዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025