የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የክልሉን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅም በተገቢው ለመጠቀም የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቶባቸዋል−ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

Mar 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤መጋቢት 15/2018 (ኢዜአ) ፡-የሲዳማ ክልልን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅምና ምቹ ዕድል በተገቢው ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ተደግፈው የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እንደተገኘባቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።

"ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የክልሉን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅም በተገቢው ለመጠቀም የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቶባቸዋል።

በዚህም ኢንዱስትሪዎችን በተደራጀ መልኩ በመደገፍ ዘርፉ በማምረት አቅምና በስራ እድል ፈጠራ አቅሙን እንዲያጎለብት ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ኢንዱስትሪዎችም ከአመራሩና ፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ዘርፉ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ማሳደግ አለባቸው ብለዋል።

በዘርፉ የተጀመሩ ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸውም የክልሉ መንግስት ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

ነዋሪዎች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መነሻ በተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ምርቶችን ከመሸመት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርትን የመጠቀም ልምድን እንዲያሳድጉም ጠይቀዋል።


የክልሉ ኢንደስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበሩ በበኩላቸው በክልሉ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ በኋላ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም መጨመሩን ገልጸዋል።

ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች መጠን በመጨመር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትም ኢኮኖሚያዊ አቅምን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አካል የሆነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ ከስራ ውጪ የነበሩ 80 ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲመለሱ እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።

በክልሉ በኢንዱስትሪው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለውን ለውጥ ለማሳየት ከ160 በላይ ኢንዱስትሪዎች የተሳተፉበት ኤግዚቢሽንና ባዛር ዛሬ በይፋ እንደሚከፈትም ነው የተናገሩት።

በኤግዚቢሽንና ባዛሩም ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር እንደሚፈጠር ጠቅሰው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጠርም ገልጸዋል።

በክልሉ ከ1 ሺህ 455 በላይ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።

በመድረኩም ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኋላ የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።

"ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛርም በርእሰ መስተዳድሩ በይፋ እንደሚከፈትም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025