🔇Unmute
ሀዋሳ ፤መጋቢት 15/2018 (ኢዜአ) ፡-የሲዳማ ክልልን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅምና ምቹ ዕድል በተገቢው ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ተደግፈው የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እንደተገኘባቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።
"ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የክልሉን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅም በተገቢው ለመጠቀም የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቶባቸዋል።
በዚህም ኢንዱስትሪዎችን በተደራጀ መልኩ በመደገፍ ዘርፉ በማምረት አቅምና በስራ እድል ፈጠራ አቅሙን እንዲያጎለብት ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ኢንዱስትሪዎችም ከአመራሩና ፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ዘርፉ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ማሳደግ አለባቸው ብለዋል።
በዘርፉ የተጀመሩ ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸውም የክልሉ መንግስት ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ነዋሪዎች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መነሻ በተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ምርቶችን ከመሸመት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርትን የመጠቀም ልምድን እንዲያሳድጉም ጠይቀዋል።

የክልሉ ኢንደስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበሩ በበኩላቸው በክልሉ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ በኋላ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም መጨመሩን ገልጸዋል።
ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች መጠን በመጨመር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትም ኢኮኖሚያዊ አቅምን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አካል የሆነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ ከስራ ውጪ የነበሩ 80 ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲመለሱ እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
በክልሉ በኢንዱስትሪው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለውን ለውጥ ለማሳየት ከ160 በላይ ኢንዱስትሪዎች የተሳተፉበት ኤግዚቢሽንና ባዛር ዛሬ በይፋ እንደሚከፈትም ነው የተናገሩት።
በኤግዚቢሽንና ባዛሩም ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር እንደሚፈጠር ጠቅሰው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጠርም ገልጸዋል።
በክልሉ ከ1 ሺህ 455 በላይ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።
በመድረኩም ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኋላ የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።
"ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛርም በርእሰ መስተዳድሩ በይፋ እንደሚከፈትም ታውቋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026