🔇Unmute
ሀዋሳ ፤መጋቢት 15/2018 (ኢዜአ) ፡-የሲዳማ ክልልን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅምና ምቹ ዕድል በተገቢው ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ተደግፈው የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እንደተገኘባቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።
"ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የክልሉን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅም በተገቢው ለመጠቀም የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቶባቸዋል።
በዚህም ኢንዱስትሪዎችን በተደራጀ መልኩ በመደገፍ ዘርፉ በማምረት አቅምና በስራ እድል ፈጠራ አቅሙን እንዲያጎለብት ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ኢንዱስትሪዎችም ከአመራሩና ፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ዘርፉ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ማሳደግ አለባቸው ብለዋል።
በዘርፉ የተጀመሩ ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸውም የክልሉ መንግስት ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ነዋሪዎች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መነሻ በተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ምርቶችን ከመሸመት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርትን የመጠቀም ልምድን እንዲያሳድጉም ጠይቀዋል።

የክልሉ ኢንደስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበሩ በበኩላቸው በክልሉ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ በኋላ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም መጨመሩን ገልጸዋል።
ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች መጠን በመጨመር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትም ኢኮኖሚያዊ አቅምን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አካል የሆነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ ከስራ ውጪ የነበሩ 80 ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲመለሱ እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
በክልሉ በኢንዱስትሪው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለውን ለውጥ ለማሳየት ከ160 በላይ ኢንዱስትሪዎች የተሳተፉበት ኤግዚቢሽንና ባዛር ዛሬ በይፋ እንደሚከፈትም ነው የተናገሩት።
በኤግዚቢሽንና ባዛሩም ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር እንደሚፈጠር ጠቅሰው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጠርም ገልጸዋል።
በክልሉ ከ1 ሺህ 455 በላይ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።
በመድረኩም ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኋላ የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።
"ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛርም በርእሰ መስተዳድሩ በይፋ እንደሚከፈትም ታውቋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025