🔇Unmute
ሀዋሳ ፤መጋቢት 15/2018 (ኢዜአ) ፡-የሲዳማ ክልልን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅምና ምቹ ዕድል በተገቢው ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ተደግፈው የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እንደተገኘባቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።
"ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የክልሉን እምቅ የኢንዱስትሪ አቅም በተገቢው ለመጠቀም የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቶባቸዋል።
በዚህም ኢንዱስትሪዎችን በተደራጀ መልኩ በመደገፍ ዘርፉ በማምረት አቅምና በስራ እድል ፈጠራ አቅሙን እንዲያጎለብት ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ኢንዱስትሪዎችም ከአመራሩና ፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ዘርፉ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ማሳደግ አለባቸው ብለዋል።
በዘርፉ የተጀመሩ ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸውም የክልሉ መንግስት ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ነዋሪዎች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መነሻ በተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ምርቶችን ከመሸመት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርትን የመጠቀም ልምድን እንዲያሳድጉም ጠይቀዋል።

የክልሉ ኢንደስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበሩ በበኩላቸው በክልሉ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ በኋላ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም መጨመሩን ገልጸዋል።
ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች መጠን በመጨመር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትም ኢኮኖሚያዊ አቅምን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አካል የሆነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ ከስራ ውጪ የነበሩ 80 ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲመለሱ እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
በክልሉ በኢንዱስትሪው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለውን ለውጥ ለማሳየት ከ160 በላይ ኢንዱስትሪዎች የተሳተፉበት ኤግዚቢሽንና ባዛር ዛሬ በይፋ እንደሚከፈትም ነው የተናገሩት።
በኤግዚቢሽንና ባዛሩም ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር እንደሚፈጠር ጠቅሰው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጠርም ገልጸዋል።
በክልሉ ከ1 ሺህ 455 በላይ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።
በመድረኩም ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኋላ የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።
"ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛርም በርእሰ መስተዳድሩ በይፋ እንደሚከፈትም ታውቋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026