የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ አገልግሎት አግኝተናል

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፡- የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ አገልግሎት ከመስጠቱ ባለፈ ለአቅመ ደካሞችም እፎይታን መስጠቱን ነዋሪዎች ገለፁ፡፡

ማዕከሉ ስራ ከጀመረ ስድስት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ነዋሪዎች ሁሉንም አገልግሎት በአንድ ማዕከል በማግኘታቸው ጊዜና ገንዘባቸውን መቆጠብ ችለዋል።

ኢዜአ ካነጋገራቸው የከተማው ተገልጋዮች መካከል አቶ ኑሪ የሱፍ፤ የውኃ እና የመብራት ክፍያዎችን ለመክፈል ከዚህ ቀደም ቀናትን ይወስድባቸው እንደነበር አስታውሰዋል።

እሁን ላይ ግን በከተማው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚፈልጉትን ክፍያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

ለነዚህ አገልግሎቶች ሲያወጡ የነበሩትን የትራንስፖርት እና ተጨማሪ ወጪዎች ማስቀረታቸውንም ይገልጻሉ።

ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሙክታር ኢብራሂም ከመሬት ይዞታ ጋር የተያያዘ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ማዕከሉ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ለመሰል አገልግሎት ወደተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች በየቀኑ ይመላለሱ እንደነበር ተናግረው አሁን በግማሽ ቀን ውስጥ ተጠናቆልኛል ብለዋል።


የጅማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት ከ84 ሺህ በላይ አገልግሎቶችን መስጠቱን የተናገሩት ደግሞ የማዕከሉ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዲ ሰለሞን ናቸው።

ወደ ማዕከሉ 25 ሴክተሮች የገቡ ሲሆን በሴክተሮቹ 135 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ጠቅሰው 103 ሠራተኞች ለማኅበረሰቡ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አንስተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞችን ያማከለ ምቹ አገልግሎትም እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

አገልግሎት ሰጪ ሠራተኞች ወደ አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞች ቀርበው ከማገልገል በተጨማሪ ልዩ የሊፍት አገልግሎት መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።

በቀጣይ በከተማዋ በሚገኙ ቀበሌዎች ቅርንጫፎችን በመክፈት ይበልጥ ወደ ማኅበረሰቡ ለመቅረብ ታቅዷል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የማዕከሉን አገልግሎት ተንቀሳቃሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን አቶ አብዲ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025