የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ አገልግሎት አግኝተናል

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፡- የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ አገልግሎት ከመስጠቱ ባለፈ ለአቅመ ደካሞችም እፎይታን መስጠቱን ነዋሪዎች ገለፁ፡፡

ማዕከሉ ስራ ከጀመረ ስድስት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ነዋሪዎች ሁሉንም አገልግሎት በአንድ ማዕከል በማግኘታቸው ጊዜና ገንዘባቸውን መቆጠብ ችለዋል።

ኢዜአ ካነጋገራቸው የከተማው ተገልጋዮች መካከል አቶ ኑሪ የሱፍ፤ የውኃ እና የመብራት ክፍያዎችን ለመክፈል ከዚህ ቀደም ቀናትን ይወስድባቸው እንደነበር አስታውሰዋል።

እሁን ላይ ግን በከተማው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚፈልጉትን ክፍያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

ለነዚህ አገልግሎቶች ሲያወጡ የነበሩትን የትራንስፖርት እና ተጨማሪ ወጪዎች ማስቀረታቸውንም ይገልጻሉ።

ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሙክታር ኢብራሂም ከመሬት ይዞታ ጋር የተያያዘ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ማዕከሉ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ለመሰል አገልግሎት ወደተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች በየቀኑ ይመላለሱ እንደነበር ተናግረው አሁን በግማሽ ቀን ውስጥ ተጠናቆልኛል ብለዋል።


የጅማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት ከ84 ሺህ በላይ አገልግሎቶችን መስጠቱን የተናገሩት ደግሞ የማዕከሉ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዲ ሰለሞን ናቸው።

ወደ ማዕከሉ 25 ሴክተሮች የገቡ ሲሆን በሴክተሮቹ 135 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ጠቅሰው 103 ሠራተኞች ለማኅበረሰቡ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አንስተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞችን ያማከለ ምቹ አገልግሎትም እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

አገልግሎት ሰጪ ሠራተኞች ወደ አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞች ቀርበው ከማገልገል በተጨማሪ ልዩ የሊፍት አገልግሎት መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።

በቀጣይ በከተማዋ በሚገኙ ቀበሌዎች ቅርንጫፎችን በመክፈት ይበልጥ ወደ ማኅበረሰቡ ለመቅረብ ታቅዷል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የማዕከሉን አገልግሎት ተንቀሳቃሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን አቶ አብዲ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026