የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እያደረገች ላለው ብርቱ ጥረት እውቅና ልሰጥ እወዳለሁ-ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዌላ (ዶ/ር)

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እያደረገች ላለው ብርቱ ጥረት እውቅና እንደሚሰጡ የድርጅቱ ዳይሬክተር ጀነራል ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዌላ (ዶ/ር) ገለጹ።

14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) የሚኒስትሮች ስብሰባ (MC14) ዛሬ በካሜሮን ያውንዴ ይካሄዳል።

በሚኒስትሮች ስብሰባው ላይ የድርጅቱ 166 አባል ሀገራት የንግድ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራው ልዑክ በስብሰባው ላይ እየተሳተፈ ነው።

የዓለም ንግድ ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራል ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዌላ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር 22 ሀገራት የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።

አንዳንድ ሀገራት አባል ለመሆን ለአስርት ዓመታት ጥረት ማድረጋቸውንና ሌሎች ሀገራት በቅርቡ ጥያቄያቸውን ማቅረባቸውን አመልክተዋል።

ከ22 ሀገራት በተጨማሪ የፋሮ ደሴቶች አባል ለመሆን ጥያቄ ያቀረበች አዲስ ሀገር መሆኗን ጠቁመው፥ጥያቄው ለድርጅቱ አጠቃላይ ምክር ቤት ገና አለመታየቱን ጠቁመዋል።

የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን አድካሚ፣ብርቱ ጥረት እና ጽናት የሚጠይቅ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ አባል ለመሆን እየጣሩ ያሉ ሀገራት ለጠንካራ ስራቸው እና ትዕግስታቸው እውቅና መስጠት እወዳለሁ ብለዋል።

ዳይሬክተ ጀነራሏ ባደረጉት ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት በስብሰባው ላይ እየተሳተፈ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ልዑክ እውቅና ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ እና ኡዝቤኪስታን እ.አ.አ በ2026 የድርጅቱ አባል እንደሚሆኑ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል ዋና ዳይሬክተሯ።

14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) የሚኒስትሮች ስብስባ (MC14) እስከ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።

በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራው ልዑክ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ ይገኛል።

ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2026 የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ድርድር ለማጠናቀቅ አቅዳ እየሰራች ትገኛለች።

የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰ ሲሆን 7ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እ.ኤ.አ በኤፕሪል ወር 2026 ለማካሄድ ኢትዮጵያ ዝግጅቷን አጠናቃለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025