የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እያደረገች ላለው ብርቱ ጥረት እውቅና ልሰጥ እወዳለሁ-ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዌላ (ዶ/ር)

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እያደረገች ላለው ብርቱ ጥረት እውቅና እንደሚሰጡ የድርጅቱ ዳይሬክተር ጀነራል ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዌላ (ዶ/ር) ገለጹ።

14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) የሚኒስትሮች ስብሰባ (MC14) ዛሬ በካሜሮን ያውንዴ ይካሄዳል።

በሚኒስትሮች ስብሰባው ላይ የድርጅቱ 166 አባል ሀገራት የንግድ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራው ልዑክ በስብሰባው ላይ እየተሳተፈ ነው።

የዓለም ንግድ ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራል ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዌላ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር 22 ሀገራት የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።

አንዳንድ ሀገራት አባል ለመሆን ለአስርት ዓመታት ጥረት ማድረጋቸውንና ሌሎች ሀገራት በቅርቡ ጥያቄያቸውን ማቅረባቸውን አመልክተዋል።

ከ22 ሀገራት በተጨማሪ የፋሮ ደሴቶች አባል ለመሆን ጥያቄ ያቀረበች አዲስ ሀገር መሆኗን ጠቁመው፥ጥያቄው ለድርጅቱ አጠቃላይ ምክር ቤት ገና አለመታየቱን ጠቁመዋል።

የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን አድካሚ፣ብርቱ ጥረት እና ጽናት የሚጠይቅ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ አባል ለመሆን እየጣሩ ያሉ ሀገራት ለጠንካራ ስራቸው እና ትዕግስታቸው እውቅና መስጠት እወዳለሁ ብለዋል።

ዳይሬክተ ጀነራሏ ባደረጉት ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት በስብሰባው ላይ እየተሳተፈ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ልዑክ እውቅና ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ እና ኡዝቤኪስታን እ.አ.አ በ2026 የድርጅቱ አባል እንደሚሆኑ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል ዋና ዳይሬክተሯ።

14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) የሚኒስትሮች ስብስባ (MC14) እስከ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።

በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራው ልዑክ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ ይገኛል።

ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2026 የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ድርድር ለማጠናቀቅ አቅዳ እየሰራች ትገኛለች።

የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰ ሲሆን 7ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እ.ኤ.አ በኤፕሪል ወር 2026 ለማካሄድ ኢትዮጵያ ዝግጅቷን አጠናቃለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026