የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን ለመግታት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ሥርዓት እየተዘረጋ ነው

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን ለመግታት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ሥርዓት እየተዘረጋ መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን አስመልክቶ በወጣው ዓመታዊ ሪፖርት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ለውጡን ተከትሎ የሀሳብ ነፃነት፣ ብዝሃነትና አካታችነት ተፈጥሯል፡፡

ዜጎች በተለያዩ አማራጮች መረጃ የሚያገኙበትና ሀሳባቸውን በነጻነት የሚያንሸራሽሩበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።

ይህንን መልካም ዕድል በአዋጅና በመመሪያ በመደገፍ ለዴሞክራሲና ለሀገር ግንባታ ለማዋል እየተሰራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ባለስልጣኑ ከሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት ጋር በተያያዘ በተለያዩ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ጥናት ሲያደርግ ቆይቷል ነው ያሉት፡፡

የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ለብሔራዊ ደህንነትና ለሀገር ሰላም፤ ለብዝሀነትና እኩልነት እንዲሁም ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አደጋ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በዚህም ባለፉት ዓመታት የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል ጥናት በማካሄድ የመፍትሄ እርምጃ ሲወሰድ ቆይቷል ብለዋል፡፡

ባለስልጣኑ በተሰጠው ሃላፊነት መሰረት ማህበራዊ ሚዲያዎች የጥላቻ ንግግር እና የሀሰት መረጃዎችን ሪፖርት በቀረበላቸው በ24 ሰዓት ውስጥ እንዲያነሱ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

በዘንድሮ ዓመት ከጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ጋር በተያያዘ የማህበራዊ ሚዲያዎች ግዴታና ሃላፊነታቸውን የተወጡበትን መንገድ የሚያሳይ ሪፖርት መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡

ዓመታዊ ሪፖርቱ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተከታይ ባላቸውና ከፍተኛ ይዘት በሚሰራጭባቸው አምስት የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆች ትኩረት ማድረጉን ጠቅሰዋል።

በአምስት ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች በቴክኖሎጂ በታገዘ የህዝብ አስተያየት መጠይቅ ተሰብስቦ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መተንተኑን ገልጸዋል፡፡

በተለይ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ታግዘው የሚሰራጩ የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ ይዘቶች ስጋት መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ ይዘቶች በሀገር ሰላምና ልማት፣ በዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ላይ ስጋት እንዳይፈጥሩ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩም አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025