የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ውጤቶችን ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ነው

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ መጋቢት 21/2018(ኢዜአ)፦ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የሚከናወኑ የጥናትና ምርምር ውጤቶች ወደ ተጠቃሚው ማህበረሰብ እንዲደርሱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገለጸ።

ዩኒቨርሲቲው ይህንን የገለጸው ''ምርምር ለማህበረሰብ ለውጥና ዘላቂ ልማት'' በሚል መሪ ሀሳብ ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ እያካሄደ ባለበት ወቅት ነው።

በመርሐግብሩ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች፣ ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ከመማር ማስተማር ተግባር ጎን ለጎን የማህበረሰቡን ችግርና ፍላጎት መሰረት ላደረጉ ጥናትና ምርምሮች ልዩ ትኩረት ሰጥቷል።

ዩኒቨርሲቲው በዋናነት በግብርና እና ምርታማነት፣ በቱሪዝም ልማት፣ በጤና ጥበቃ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቀደም ሲል በተናጠል ይከናወኑ የነበሩ ጥናቶች አሁን ላይ ተቀናጅተው ጠንካራ ውጤት እንዲያመጡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህ ዓመታዊ አውደ ጥናት ላይም በተለያዩ ዘርፎች የተጠኑ 42 የምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ጥናቶቹ በወረቀት ላይ ብቻ እንዳይቀሩ ከመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤቶችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅት መፈጠሩን ምክትል ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።

ይህም የጥናትና ምርምር ውጤቶች ወደ ማህበረሰብ ፕሮጀክት ተቀይረው ህዝቡን በቀጥታ ተጠቃሚ እንዲያደርጉ ያስችላል ብለዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሀንድሶ(ዶ/ር) በበኩላቸው በበይነመረብ (ቨርቹዋል) ባስተላለፉት መልዕክት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን የምርምር ውጤቶች ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ የጀመሩትን ጥረት ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ለዚህም ተመራማሪዎች አቅማቸውን በማጎልበትና ምቹ መደላድሎችን በመጠቀም ውጤታማ ስራ ሊሰሩ እንደሚገባ አመልክተዋል።

የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎችም እንዲህ ያሉ መድረኮች ተመራማሪዎችና ተጠቃሚ አካላት ተቀራርበው በችግሮች ላይ እንዲመካከሩ በማድረጋቸው፣ ለችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ጉልህ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026