የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ውጤቶችን ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ነው

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ መጋቢት 21/2018(ኢዜአ)፦ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የሚከናወኑ የጥናትና ምርምር ውጤቶች ወደ ተጠቃሚው ማህበረሰብ እንዲደርሱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገለጸ።

ዩኒቨርሲቲው ይህንን የገለጸው ''ምርምር ለማህበረሰብ ለውጥና ዘላቂ ልማት'' በሚል መሪ ሀሳብ ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ እያካሄደ ባለበት ወቅት ነው።

በመርሐግብሩ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች፣ ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ከመማር ማስተማር ተግባር ጎን ለጎን የማህበረሰቡን ችግርና ፍላጎት መሰረት ላደረጉ ጥናትና ምርምሮች ልዩ ትኩረት ሰጥቷል።

ዩኒቨርሲቲው በዋናነት በግብርና እና ምርታማነት፣ በቱሪዝም ልማት፣ በጤና ጥበቃ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቀደም ሲል በተናጠል ይከናወኑ የነበሩ ጥናቶች አሁን ላይ ተቀናጅተው ጠንካራ ውጤት እንዲያመጡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህ ዓመታዊ አውደ ጥናት ላይም በተለያዩ ዘርፎች የተጠኑ 42 የምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ጥናቶቹ በወረቀት ላይ ብቻ እንዳይቀሩ ከመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤቶችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅት መፈጠሩን ምክትል ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።

ይህም የጥናትና ምርምር ውጤቶች ወደ ማህበረሰብ ፕሮጀክት ተቀይረው ህዝቡን በቀጥታ ተጠቃሚ እንዲያደርጉ ያስችላል ብለዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሀንድሶ(ዶ/ር) በበኩላቸው በበይነመረብ (ቨርቹዋል) ባስተላለፉት መልዕክት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን የምርምር ውጤቶች ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ የጀመሩትን ጥረት ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ለዚህም ተመራማሪዎች አቅማቸውን በማጎልበትና ምቹ መደላድሎችን በመጠቀም ውጤታማ ስራ ሊሰሩ እንደሚገባ አመልክተዋል።

የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎችም እንዲህ ያሉ መድረኮች ተመራማሪዎችና ተጠቃሚ አካላት ተቀራርበው በችግሮች ላይ እንዲመካከሩ በማድረጋቸው፣ ለችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ጉልህ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026