🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018(ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግሥት በኢንዱስትሪው ዘርፍ ያስመዘገባቸው ስኬቶች የስራ እድል ተጠቃሚ መሆን የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው በተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚሰሩ ሙያተኞች ገለጹ።
ከለውጡ ወዲህ መንግሥት የኢንዱስትሪ ዘርፉን የሚያነቃቁ በርካታ ማሻሻያዎችን በማድረግ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅምንና ተኪ ምርትን የሚያሳድጉ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ሌሎች ሰፋፊ ተግባራት ተከናውነዋል።
በዚህም ለሀገር ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ጉልህ ድርሻ የሚጫወተውን የኢንዱስትሪ ዘርፉን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የፖሊሲ ለውጥን ጨምሮ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን በማስጀመር በዘርፉ እመርታዊ ለውጥ ማስመዝገብ ተችሏል።
በተከናወኑ ተግባራትም ሀገሪቱ ከውጭ የምታስገባቸውን ልዩ ልዩ ተኪ ምርቶች በሀገር ውስጥ ምርት የሚተካበትንና የውጭ ምንዛሬ የምታገኝበት ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል።
በዚህም በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪዎች አማካይ የማምርት አቅም 66 ነጥብ 3 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህም ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር የስራ አጥነትን ለመቅረፍ እንደ ሀገር የሚከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አወንታዊ አበርክቶ እያስገኘ ነው።

በተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የስራ እድል ከተፈጠረላችው ወጣቶች መካከል ወጣት ሰኚ ገለታ ለኢዜአ እንደተናገረው ከከፍተኛ የትምህርት ተቋም በኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ በ2017 ዓ.ም መመረቁን አስታውሶ አሁን በዳቺ ማኑፋክቸሪንግ በምርት ተቆጣጣሪ ባለሙያነት እያገለገለ ይገኛል።
በድርጅቱ የስራ እድል ተጠቃሚ መሆኑ ከኢትዮጵያውያን ብሎም ከውጭ ባለሙያዎች በትምህርት የጨበጠውን እውቀት ይበልጥ የሚያሳድግበት ክህሎት እንዲያገኝ እንደረዳው ገልጿል።

በኬርመንት ጋርመንት የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ ያሉት ዓለም ሙላቱ በበኩላቸው፤ በኢንዱስትሪው በተፈጠረላቸው የስራ እድል ለበርካታ ዓመታት ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በዘመኑ ታከለ እና ጓደኞቻቸው ሳሙና አምራች ሽርክና ማህበር የጥራት ቁጥጥር ባለሙያ የሆኑት ብሩክ አሰፋ በበኩላቸው፤ ዜጎች የስራ እድል ተጠቃሚነታቸውን ለማጠናከር በመንግስት በኩል የተጀመሩ ኢንዱስትሪዎችን የመደገፍ ስራ መጠናከር እንዳለበት ጠይቀዋል።

ወጣት እዮብ ደሬሳ በበኩሉ ከለውጡ ወዲህ በሀገሪቱ የኢንዱስሪዎች መጠናከርና መስፋፋት ከከፍተኛ ትምህርት ተመርቀው እንደወጡ በሙያቸው መስራት የሚችሉበትን የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስችሎኛል ብሏል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማሳደግ አምራች የሰው ሀይል ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንዱስትሪ ዘርፉን በሚፈለገው ደረጃ ለማሳደግ በዘርፉ ዜጎችን ማብቃት እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በየዓመቱ በአማካኝ 350 ሺህ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ እየተቻለ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስቴሩ የኢንዱስትሪው ዘርፍ የዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚነት ያረጋገጠ እንዲሆን ዘርፉ ላይ ያሉ ማነቆዎችን የመፍታት ስራ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025