የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በምዕራብ አፍሪካ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል ለመገንባት የተግባር ምዕራፍ ላይ ደርሷል

Apr 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በምዕራብ አፍሪካ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል ለመገንባት የአዋጭነት ጥናቱን አጠናቆ የተግባር ምዕራፍ ላይ መድረሱን የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለጹ፡፡

በአዲስ አበባ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአፍሪካ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን ኮንፍረንስ 2026 ዛሬ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በኮንፍረሱና በሌሎች የአየር መንገዱ ወቅታዊ አንቅስቃሴዎች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ዋና ሥራ አስፈፃሚው በማብራሪያቸው፤ የተሟላ የጥገና፣ እድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ስኬታማ አየር መንገድ መገንባት ያስችላል ብለዋል።

በአፍሪካ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ክፍተት ያለበት በመሆኑ የአየር መንገዶችም ደካማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአፍሪካ ጠንካራ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ለመስጠት ሰፊ ሀብትና ዕውቀት ይፈልጋል ያሉት አቶ መስፍን፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የአፍሪካ አየር መንገዶች በትብብር መስራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

አፍሪካ ዕምቅ አቅም ያላቸው ወጣቶች እንዳሏት ገልጸው፤ ወጣቶችን አሰልጥኖ ማሰማራት ይገባል ብለዋል።

በተለያዩ ዓለማት ካሉ የአየር መንገድ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን ተቋማት ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ለብዙ ዓመታት ሰርቻለሁ ያሉት አቶ መስፍን፤ የአውሮፕላን ጥገና ክፍል ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የስኬት ቁልፍ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስኬት ምስጢር በአየር መንገዱ ያለው የተሟላ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላን ጥገና ክፍል ለአፍሪካና ለሌሎች ዓለም ሀገራት አውሮፕላኖች ጭምር የጥገና አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልጸው፤ ኮንፍረንሱ የአየር መንገዱን አቅም ለአፍሪካውያን ያሳየንበት መድረክ ነው ብለዋል፡፡

ከዚህም ባለፈ አስካይ ከተባለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አጋር ጋር በመተባበር ምዕራብ አፍሪካ ላይ የጥገና ማዕከል ለመክፈት የአዋጭነት ጥናቱን አጠናቆ ወደ ተግባር ለመግባት በዝግጅት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በረራ ያቋረጠባቸው ከተሞች እንደነበሩ አስታውሰው፤ የቀጣናው ሀገራት አየር መንገዶች በረራ በመጀመራቸውና አየር መንገዱ የራሱን የድህንነት ግምገማ በማድረግ በአምስት ከተሞች በረራ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡

የቀጣናውን የጸጥታ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸው፤ ሁኔታውን እያየን ወደ ነበርንበት መደበኛ የበረራ ሥራችን እንመለሳለን ነው ያሉት፡፡

በአፍሪካና ሌሎች ዓለማት መካከል ያለውን መንገደኛ ጨምሮ ብዙ መንገደኞችን እናጓጉዝ ነበር ያሉት አቶ መስፍን፤ የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ሌሎች አማራጮችን እንዲያዩ አድርጓቸዋል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026