የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በለውጡ አመታት በድሬደዋ አስተዳደር በተከናወኑ የልማት ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦ በለውጡ አመታት በድሬደዋ አስተዳደር የተከናወኑ የልማትና ሰላም ተግባራት ውጤት መመዝገባቸውን በብልፅግና ፓርቲ የድሬደዋ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ተናገሩ።

የድሬደዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በለውጡ አመታት የተሰሩ የልማትና ሰላም ጉዳዮች ላይ ዛሬ ተወያይተዋል።

ውይይቱን የመሩት በብልጽግና ፓርቲ የድሬደዋ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በወቅቱ፤ የለውጡ አመራር ህዝብን በማሳተፍ ሀገርንና ድሬደዋን የሚያሻግሩ ተጨባጭ ልማትን አስመዝግቧል ብለዋል።

በለውጡ አመታት በመደመር እሳቤ የተከናወኑ በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ውጤት መምጣቱንም አስረድተዋል።

በድሬደዋ ገጠርና ከተማ የተተገበሩ የልማት ተግባራት ከተረጂነት ወደ አምራችነት እያሸጋገሩና ድህነትን በተጨባጭ እየቀነሱ እንደሚገኙም አንስተዋል።

በተለይም በከተማ በአምራች ኢንዱስትሪው፣ በኮሪደር ልማት፣ በቱሪዝም፣ በስራ ዕድል ፈጠራ የተሰሩ ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ መሆናቸውን በመግለፅ።

በገጠር ቀበሌዎችም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃን በተቀናጀ መንገድ በማከናወን ለግብርና ምርትና ምርታማነት መጎልበት መሠረታዊ መደላድል የፈጠሩ ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።

ይህን ምቹ መደላድል በመጠቀም የአነስተኛ መስኖና የመጠጥ ውሃ በማስፋፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ የፍራፍሬ ምርትን በላቀ ደረጃ በማጎልበት፣ በሌማት ትሩፋት የእንሰሳት ምርታማነትን በመጨመር ማህበረሰቡን ከተረጂነት ወደ አምራችነት የማሸጋገሩ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉ ከፍተኛ አመራሮች በበኩላቸው ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በድሬደዋ ገጠርና ከተማ የተከናወኑ የሰላም፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ እያረጋገጡ መሆናቸውን አንስተዋል።

በስምንቱ የለውጥ አመታት የተከናወኑ ሁለንተናዊ ልማቶች ድሬደዋ የብልጽግና ትልሞች የተሳካባት ቀዳሚ አካባቢ እንድትሆን አስቻይ ወረቶች የተፈጠረባት መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የተጀመሩትን አበረታች ውጤቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሻገር የተቀናጀ ርብርብ እንደሚያደርጉም አመራሮቹ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026