የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በለውጡ አመታት በድሬደዋ አስተዳደር በተከናወኑ የልማት ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦ በለውጡ አመታት በድሬደዋ አስተዳደር የተከናወኑ የልማትና ሰላም ተግባራት ውጤት መመዝገባቸውን በብልፅግና ፓርቲ የድሬደዋ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ተናገሩ።

የድሬደዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በለውጡ አመታት የተሰሩ የልማትና ሰላም ጉዳዮች ላይ ዛሬ ተወያይተዋል።

ውይይቱን የመሩት በብልጽግና ፓርቲ የድሬደዋ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በወቅቱ፤ የለውጡ አመራር ህዝብን በማሳተፍ ሀገርንና ድሬደዋን የሚያሻግሩ ተጨባጭ ልማትን አስመዝግቧል ብለዋል።

በለውጡ አመታት በመደመር እሳቤ የተከናወኑ በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ውጤት መምጣቱንም አስረድተዋል።

በድሬደዋ ገጠርና ከተማ የተተገበሩ የልማት ተግባራት ከተረጂነት ወደ አምራችነት እያሸጋገሩና ድህነትን በተጨባጭ እየቀነሱ እንደሚገኙም አንስተዋል።

በተለይም በከተማ በአምራች ኢንዱስትሪው፣ በኮሪደር ልማት፣ በቱሪዝም፣ በስራ ዕድል ፈጠራ የተሰሩ ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ መሆናቸውን በመግለፅ።

በገጠር ቀበሌዎችም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃን በተቀናጀ መንገድ በማከናወን ለግብርና ምርትና ምርታማነት መጎልበት መሠረታዊ መደላድል የፈጠሩ ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።

ይህን ምቹ መደላድል በመጠቀም የአነስተኛ መስኖና የመጠጥ ውሃ በማስፋፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ የፍራፍሬ ምርትን በላቀ ደረጃ በማጎልበት፣ በሌማት ትሩፋት የእንሰሳት ምርታማነትን በመጨመር ማህበረሰቡን ከተረጂነት ወደ አምራችነት የማሸጋገሩ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉ ከፍተኛ አመራሮች በበኩላቸው ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በድሬደዋ ገጠርና ከተማ የተከናወኑ የሰላም፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ እያረጋገጡ መሆናቸውን አንስተዋል።

በስምንቱ የለውጥ አመታት የተከናወኑ ሁለንተናዊ ልማቶች ድሬደዋ የብልጽግና ትልሞች የተሳካባት ቀዳሚ አካባቢ እንድትሆን አስቻይ ወረቶች የተፈጠረባት መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የተጀመሩትን አበረታች ውጤቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሻገር የተቀናጀ ርብርብ እንደሚያደርጉም አመራሮቹ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026