የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመልሱ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለህዝቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ ገለጹ።

በጅማ ዞን ኦሞ ናዳ ወረዳ አሰንዳቦ ከተማ፣ በወረዳ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።


አቶ ነመራ ቡሊ በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ በስፋት እየተተገበረ መሆኑንና የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በሂደት ለመመለስ እየተከናወነ ያለ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።


አገልግሎቱ ብልሹ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ፣ የህዝቡን ጥያቄዎች አንድ በአንድ እየመለስን ለመሆናችን ማሳያ ነው ያሉት ኃላፊው፣ ወደፊትም አገልግሎቱን በማዘመን ለበርካታ ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።


የጅማ ዞን አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፣ የዞኑ ነዋሪዎች በተደጋጋሚ የሚያነሷቸውን የልማትና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥያቄዎችን ለመፍታት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በወረዳ ደረጃ እየተስፋፋ መሆኑን ገልጸዋል።


የአሰንዳቦ ከተማ አስተዳዳሪ ነዚፍ ሼህ ከማል በማዕከሉ 11 ተቋማት 52 ዓይነት አገልግሎቶች በ8 መስኮቶች እንደሚሰጥ ጠቅሰው ባለሙያዎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ስልጠና ወስደው ወደ ስራ ገብተዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026