🔇Unmute
አሶሳ፤ ሚያዚያ 3/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ የሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በላቀ ትጋት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።
ሚኒስትሯ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችንና የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት ማብራሪያ እንደገለፁት፤ መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚያከናውናቸው የልማት ፕሮጀክቶች በፈጠራና ፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በአሶሳ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውብ ገፅታ ከማላበሱ ባለፈ ዘመናዊ ከማድረግ አንጻር የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስራ እንቅስቃሴን የጎበኙት ሚኒስትሯ ኮሌጁ አካባቢውን መሠረት ያደረገ የፈጠራ ስራ ላይ በመሠማራት ህብረተሰቡ የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመረውን የተግባር ስራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል።
ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ባለፈ ክህሎት ሽግግርና ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሯ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ከህሎት መር እሳቤን ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ሚኒስትሯ በተጨማሪም በአሶሳ ከተማ የሚገኘውን የግራናይት ፋብሪካ የስራ እንቅስቃሴ የተመለከቱ ሲሆን ፋብሪካው በአካባቢው የሚገኘውን የግራናይት ማዕደን እሴት ተጨምሮበት ለገበያ እንዲውል በማድረግ እያከናወነ የሚገኘው ጅምር ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ሚኒስትሯ በሆሞሻ ወረዳ የሚገኘውን የፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት ድርጅት፣ የገጠር ኮሪደር ልማት እና ሌሎች የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሲሆን በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች በላቀ ትጋት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።
በጉብኝቱ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻደሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025