የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ የሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በላቀ ትጋት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሚያዚያ 3/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ የሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በላቀ ትጋት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።

ሚኒስትሯ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችንና የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት ማብራሪያ እንደገለፁት፤ መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚያከናውናቸው የልማት ፕሮጀክቶች በፈጠራና ፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በአሶሳ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውብ ገፅታ ከማላበሱ ባለፈ ዘመናዊ ከማድረግ አንጻር የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስራ እንቅስቃሴን የጎበኙት ሚኒስትሯ ኮሌጁ አካባቢውን መሠረት ያደረገ የፈጠራ ስራ ላይ በመሠማራት ህብረተሰቡ የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመረውን የተግባር ስራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል።

ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ባለፈ ክህሎት ሽግግርና ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሯ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ከህሎት መር እሳቤን ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ሚኒስትሯ በተጨማሪም በአሶሳ ከተማ የሚገኘውን የግራናይት ፋብሪካ የስራ እንቅስቃሴ የተመለከቱ ሲሆን ፋብሪካው በአካባቢው የሚገኘውን የግራናይት ማዕደን እሴት ተጨምሮበት ለገበያ እንዲውል በማድረግ እያከናወነ የሚገኘው ጅምር ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ሚኒስትሯ በሆሞሻ ወረዳ የሚገኘውን የፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት ድርጅት፣ የገጠር ኮሪደር ልማት እና ሌሎች የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሲሆን በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች በላቀ ትጋት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

በጉብኝቱ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻደሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026