የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ የሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በላቀ ትጋት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሚያዚያ 3/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ የሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በላቀ ትጋት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።

ሚኒስትሯ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችንና የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት ማብራሪያ እንደገለፁት፤ መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚያከናውናቸው የልማት ፕሮጀክቶች በፈጠራና ፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በአሶሳ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውብ ገፅታ ከማላበሱ ባለፈ ዘመናዊ ከማድረግ አንጻር የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስራ እንቅስቃሴን የጎበኙት ሚኒስትሯ ኮሌጁ አካባቢውን መሠረት ያደረገ የፈጠራ ስራ ላይ በመሠማራት ህብረተሰቡ የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመረውን የተግባር ስራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል።

ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ባለፈ ክህሎት ሽግግርና ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሯ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ከህሎት መር እሳቤን ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ሚኒስትሯ በተጨማሪም በአሶሳ ከተማ የሚገኘውን የግራናይት ፋብሪካ የስራ እንቅስቃሴ የተመለከቱ ሲሆን ፋብሪካው በአካባቢው የሚገኘውን የግራናይት ማዕደን እሴት ተጨምሮበት ለገበያ እንዲውል በማድረግ እያከናወነ የሚገኘው ጅምር ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ሚኒስትሯ በሆሞሻ ወረዳ የሚገኘውን የፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት ድርጅት፣ የገጠር ኮሪደር ልማት እና ሌሎች የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሲሆን በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች በላቀ ትጋት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

በጉብኝቱ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻደሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026