የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ዕውን ለማድረግ የኮሜሳ አባል ሀገራት ያላቸውን የጋራ ትብብር ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ዕውን ለማድረግ የኮሜሳ አባል ሀገራት ያላቸውን የጋራ ትብብር ይበልጥ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ኸይረዲን ጥሪ አቀረቡ።

በስርዓተ ጾታ እኩልነትና የሴቶች ተጠቃሚነት ላይ ትኩረቱን ያደረገው 15ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ሴክሬታሪያት የቴክኒካል ኮሚቴ አህጉራዊ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ኸይረዲን በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስትራቴጂ ተቀርፆ ወደ ተግባር ተገብቷል።

በዚህም በግብርና፣ በኢንዱስትሪ ዘርፎች በስራ እድል ፈጠራ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል።

ሴቶች በንግድ ዘርፍ ላይ በሚፈለገው ደረጃ ሰርተው መለወጥ እንዳይችሉ ማነቆ ከሆኑ ተግዳሮቶች መካከል የፋይናንስ እና የመሥሪያ ቦታ ችግር ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህን ለመፍታት መንግስት የሚመለከታቸውን አካላት ያሳተፈ ተግባር እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል።

የአፍሪካውያን ሴቶችን በንግድ ስርዓቱ ላይ ተሳታፊና እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ በትብብር መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡

ሴቶች በንግድ ላይ ለመሳተፍ ማነቆ የሆኑባቸውን ተግዳሮት በመፍታት ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የኮሜሳ አባል ሀገራት ተቀራርበን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም የኮሜሳ አባል ሀገራት ያላቸውን ቅንጅታዊ ስራ በይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል።


የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ረዳት ፀሀፊ አምባሳደር ማህመድ ካዳ በበኩላቸው፤ የሥርዓተ ፆታ እኩልነትንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት ልማትን ከማሳለጥ ባለፈ አሁጉራዊ ትስስርን የበለጠ ለማጠናከር ያስችላል።

ኮሜሳ ሴቶች በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ያላቸውን የስርአተ ጾታ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚወጡ አሰራሮችን ለመደገፍ የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በአፍሪካ ሴቶች የፋይናንስ፣ የዲጂታል ክህሎት፣ የገበያ፣ የውሳኔ ሰጪነት ያላቸውን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል።


በኮሜሳ ሴክረተሪያት ሲኒየር ጀንደር ሜንስትሪሚንግ ኦፊሰር አንደር ጀንደር ኤንድ ሶሻል አፊር ሴክሬታሪያት ፅጌ ታደለ በበኩላቸው፤ በኮሜሳ አባል ሀገራት ላይ ሴቶችና ወጣቶች በኢኮኖሚያዊ ተግባራት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ በማጎልበት ፍትሀዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026