🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ዕውን ለማድረግ የኮሜሳ አባል ሀገራት ያላቸውን የጋራ ትብብር ይበልጥ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ኸይረዲን ጥሪ አቀረቡ።
በስርዓተ ጾታ እኩልነትና የሴቶች ተጠቃሚነት ላይ ትኩረቱን ያደረገው 15ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ሴክሬታሪያት የቴክኒካል ኮሚቴ አህጉራዊ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ኸይረዲን በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስትራቴጂ ተቀርፆ ወደ ተግባር ተገብቷል።
በዚህም በግብርና፣ በኢንዱስትሪ ዘርፎች በስራ እድል ፈጠራ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል።
ሴቶች በንግድ ዘርፍ ላይ በሚፈለገው ደረጃ ሰርተው መለወጥ እንዳይችሉ ማነቆ ከሆኑ ተግዳሮቶች መካከል የፋይናንስ እና የመሥሪያ ቦታ ችግር ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህን ለመፍታት መንግስት የሚመለከታቸውን አካላት ያሳተፈ ተግባር እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል።
የአፍሪካውያን ሴቶችን በንግድ ስርዓቱ ላይ ተሳታፊና እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ በትብብር መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
ሴቶች በንግድ ላይ ለመሳተፍ ማነቆ የሆኑባቸውን ተግዳሮት በመፍታት ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የኮሜሳ አባል ሀገራት ተቀራርበን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም የኮሜሳ አባል ሀገራት ያላቸውን ቅንጅታዊ ስራ በይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል።

የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ረዳት ፀሀፊ አምባሳደር ማህመድ ካዳ በበኩላቸው፤ የሥርዓተ ፆታ እኩልነትንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት ልማትን ከማሳለጥ ባለፈ አሁጉራዊ ትስስርን የበለጠ ለማጠናከር ያስችላል።
ኮሜሳ ሴቶች በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ያላቸውን የስርአተ ጾታ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚወጡ አሰራሮችን ለመደገፍ የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በአፍሪካ ሴቶች የፋይናንስ፣ የዲጂታል ክህሎት፣ የገበያ፣ የውሳኔ ሰጪነት ያላቸውን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል።

በኮሜሳ ሴክረተሪያት ሲኒየር ጀንደር ሜንስትሪሚንግ ኦፊሰር አንደር ጀንደር ኤንድ ሶሻል አፊር ሴክሬታሪያት ፅጌ ታደለ በበኩላቸው፤ በኮሜሳ አባል ሀገራት ላይ ሴቶችና ወጣቶች በኢኮኖሚያዊ ተግባራት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ በማጎልበት ፍትሀዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026