የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የመደመር ዕሳቤ ውጤት የሆነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ለአካባቢው የብልፅግና ተስፋን ይዞ መጥቷል

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር ዕሳቤ ውጤት የሆነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ለአካባቢው የብልፅግና ተስፋን ይዞ መጥቷል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ"ገበታ ለትውልድ" ኢኒሼቲቭ ተገንብቶ የተመረቀው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በዛሬው ዕለት በይፋ ሥራ ጀምሯል።


ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማስጀመሪያ መርኃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ የመደመር ዕሳቤ ውጤትና ኢትዮጵያውያን በአንድነት ከቆሙ ህልሞቻቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ማሳያ ነው።

ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ላገዙ የፀጥታ ኃይሎች፣ የአካባቢው አመራሮችና ለሕዝቡ ምስጋና ያቀረቡት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተለይም ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ ላሳዩት አርአያነት ያለው ተግባር ከፍተኛ አድናቆት ሰጥተዋል።

አቶ በላይነህ በሪዞርቱ ቅጥር ግቢ የነበረውን ጫት በሙዝ፣ በፓፓያና በቡና መተካታቸውና ለአካባቢው አርሶ አደሮችም የሙዝ ችግኝ በነጻ ማከፋፈላቸው ትልቅ ትምህርት የሚወሰድበት መሆኑን ጠቁመዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወሎ የኢትዮጵያ የአንድነትና የብዝኃነት ተምሳሌት መሆኑን ጠቅሰው፤ ​"ወሎ ማለት ኅብር ማለት ነው፤ ታሪኩ፣ ባህሉ፣ እምነቱ፣ ቋንቋው፣ ዜማው፣ ገበያው፣ መልክአ ምድሩ ኅብር ነው" ብለዋል።

ሪዞርቱ ከአንኮበር፣ ላሊበላ፣ አክሱም እና ኤርታሌ ለሚጓዙ ቱሪስቶች እንደ ስበት ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን፤ ሌሎች ባለሀብቶችም መሰል የቱሪስት መዳረሻዎችን እንዲያለሙ ጥሪ አቅርበዋል።

አካባቢው በግብርና ምርታማነት ሊለወጥ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።


ከቆቦ እስከ መካነ ሰላም እንዲሁም ከዋግ እስከ አጣዬ ለም መሬትና የውኃ ጸጋ መኖሩን ጠቅሰው፤ አካባቢው ወደ አትክልትና ፍራፍሬ ምርታማነት መሸጋገር እንዳለበት አሳስበዋል።

ተግተን ከሠራንና ፀጋዎቻችንን ካለማን የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ጉዞን እናሳካለን ብለዋል።

የልማት ውጤቶች የተመዘገቡት ሰላም በመኖሩ መሆኑን በመጥቀስ፤ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ሰላምን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ ብለዋል።

እንዲሁም መጭው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026