የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የመደመር ዕሳቤ ውጤት የሆነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ለአካባቢው የብልፅግና ተስፋን ይዞ መጥቷል

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር ዕሳቤ ውጤት የሆነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ለአካባቢው የብልፅግና ተስፋን ይዞ መጥቷል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ"ገበታ ለትውልድ" ኢኒሼቲቭ ተገንብቶ የተመረቀው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በዛሬው ዕለት በይፋ ሥራ ጀምሯል።


ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማስጀመሪያ መርኃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ የመደመር ዕሳቤ ውጤትና ኢትዮጵያውያን በአንድነት ከቆሙ ህልሞቻቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ማሳያ ነው።

ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ላገዙ የፀጥታ ኃይሎች፣ የአካባቢው አመራሮችና ለሕዝቡ ምስጋና ያቀረቡት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተለይም ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ ላሳዩት አርአያነት ያለው ተግባር ከፍተኛ አድናቆት ሰጥተዋል።

አቶ በላይነህ በሪዞርቱ ቅጥር ግቢ የነበረውን ጫት በሙዝ፣ በፓፓያና በቡና መተካታቸውና ለአካባቢው አርሶ አደሮችም የሙዝ ችግኝ በነጻ ማከፋፈላቸው ትልቅ ትምህርት የሚወሰድበት መሆኑን ጠቁመዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወሎ የኢትዮጵያ የአንድነትና የብዝኃነት ተምሳሌት መሆኑን ጠቅሰው፤ ​"ወሎ ማለት ኅብር ማለት ነው፤ ታሪኩ፣ ባህሉ፣ እምነቱ፣ ቋንቋው፣ ዜማው፣ ገበያው፣ መልክአ ምድሩ ኅብር ነው" ብለዋል።

ሪዞርቱ ከአንኮበር፣ ላሊበላ፣ አክሱም እና ኤርታሌ ለሚጓዙ ቱሪስቶች እንደ ስበት ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን፤ ሌሎች ባለሀብቶችም መሰል የቱሪስት መዳረሻዎችን እንዲያለሙ ጥሪ አቅርበዋል።

አካባቢው በግብርና ምርታማነት ሊለወጥ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።


ከቆቦ እስከ መካነ ሰላም እንዲሁም ከዋግ እስከ አጣዬ ለም መሬትና የውኃ ጸጋ መኖሩን ጠቅሰው፤ አካባቢው ወደ አትክልትና ፍራፍሬ ምርታማነት መሸጋገር እንዳለበት አሳስበዋል።

ተግተን ከሠራንና ፀጋዎቻችንን ካለማን የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ጉዞን እናሳካለን ብለዋል።

የልማት ውጤቶች የተመዘገቡት ሰላም በመኖሩ መሆኑን በመጥቀስ፤ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ሰላምን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ ብለዋል።

እንዲሁም መጭው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026