የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረጉ ነው

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በድሬዳዋ አስተዳደር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለህዝብ ተጠቃሚነት ልዩ ትኩረት በመስጠት ሰው ተኮር የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ28 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል እንደተፈጠረም ተገልጿል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የአስፈፃሚውን የበጀት ዓመቱን ዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም እና የመጪው በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ እየተወያዩ ነው።


የስራ አፈፃፀሙን ግምገማ እየመሩ የሚገኙት የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር በወቅቱ፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን በተቀናጀ መንገድ በማከናወን የህዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።

በተለይም በስራ ዕድል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር፣ በገጠርና በከተማ የመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ በኮሪደር ልማት እንዲሁም በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በአስተዳደሩ የተከናወኑ ተግባራት በአብነት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተከናወኑ ስራዎችም 56 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎች ከልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ሽግግር ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተሰሩ ስራዎችም ውጤታማ መሆናቸውን አንስተው በአስተዳደሩ ገጠርና ከተማ ቀበሌዎች ዘመናዊ የእህል ማከማቻ መጋዘኖች ተገንብተው እህል መከማቸቱን አንስተዋል።

በተጨማሪም ከ45 ሚሊዮን ብር በላይ ለዚሁ ዓላማ ይውል ዘንድ መሰብሰቡን በማስታወስ።

እነዚህን ውጤታማ ስራዎች በበለጠ ለማሳደግ በቀጣይ ወራት ርብርቡ ይጠናከራል ብለዋል ከንቲባው።

የአስፈፃሚውን የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ለተወያዮች ያቀረቡት የአስተዳደሩ ፕላንና ኢኮኖሚ ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኃይለማሪያም ዳዲ ናቸው።


ኮሚሽነር ኃይለማሪያም እንዳሉት፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ28 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል በመፍጠር የወጣቶችን መሠረታዊ ጥያቄዎች መፍታት ተችሏል።

የስራ ዕድል ከተፈጠረላቸው መካከል 16 ሺህ የሚጠጉት በቋሚነት የስራ ዕድል ያገኙ መሆናቸውን አንስተዋል።

በተለይም ባለፉት ዘጠኝ ወራት የገጠርና የከተማውን ነዋሪዎች መሠረታዊ የልማት ጥያቄዎች በተጨባጭ የሚፈቱ 147 ነባርና አዳዲስ ፕሮጀክቶች በተሻለ አፈፃፀም ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025