የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ ዲጂታላይዝ ማድረግ ፈጣን አገልግሎትን ለመስጠት ያስችላል

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን/ኮምቦልቻ፤ሚያዝያ 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ ዲጂታላይዝ የማድረግ ተግባሩ ፈጣን አገልግሎትን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ ⵆ

ቢሮው ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች የመረጃ ማረጋገጥ ሥራን የተመለከተ የምክክር መድረክ በደብረ ብርሃንና ኮምቦልቻ ከተሞች አካሄዷል።

የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአደረጃጀት ስራ ምዘናና ክፍያ ጥናት ዳይሬክተር አቶ አንተነህ ይስማው፤ በደብረ ብርሃን መድረክ እንደገለጹት የዲጂታላይዜሽን ትግበራው የሲቪል ሰርቪስ ግንባታን ለማፋጠን የሚያስችል ነው።


ይህም የመንግስት ሰራተኛውን በጠራ መረጃ ላይ በመመስረት መብትና ጥቅሙን በፍትሃዊነት በማሳደግ የስራ ተነሳሽነቱን ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ስርዓቱ ህግ አውጪና ህግ አስፈፃሚ አካላት በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርተው እንዲወስኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።


የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ካሱ አበባው፤ በኮምቦልቻ ከተማ በተካሄደው መድረክ ላይ እንደገለፁት፣ የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ በማጥራትና ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተሰራ ነው።


በክልሉ የሚገኙ ከ560 ሺህ በላይ የመንግስት ሰራተኞችን በመረጃ አያያዝ ስርዓት ወደ አንድ ቋት በማስገባት ፈጣንና ተደራሽነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት መደረጉን አንስተዋል።

መረጃውን ዲጂታላይዝ የማድረግ ጥረቱ በአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ መሰረት የሰራተኞችን መረጃ በማጥራት ፍትሃዊ የደሞዝ ጭማሪ፣ የደረጃ እድገትና ምደባ በመስጠት መብትና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ያስችላል ብለዋል።

በተጨማሪም ተጠያቂነት ያለው፣ ፈጣንና ፍትሃዊ አገልግሎት ለህብረተሰቡ በመስጠት የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ዓይነተኛ ሚና እንደሚኖረውም አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የደሴ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኡስማን መሀመድ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከግንቦት ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ወራት የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ የማጥራት ስራ ይሰራል።


በዚህም ለመረጃ ሰብሳቢዎችና ለባለድርሻ አካላት ስልጠና በመስጠት ግንዛቤ መፈጠሩን ጠቁመው፣ መረጃውን በጥንቃቄ በመያዝ ወደ ሲስተም ለማስገባትና ዲጂታል ለማድረግ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል።

ቆጠራው በስራ ላይ የሌሉ ሰራተኞችን ለመለየት፣ ከአንድ ተቋም በላይ የሚሰሩትንና የሰራተኞችን የትምህርት ደረጃ ለመለየት ለቀጣይ ስራ ዝግጁ ለማድረግ እንደሚረዳም ተናግረዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በሪሁን ተገኝ በበኩላቸው፤መረጃ ለማጥራት የሚያስችሉ ባለሙያዎች ተለይተው ቴክኒካል ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን ጠቁመዋል።


በከተሞቹ በተካሄዱ መድረኮችም ከፌዴራል፣ ከክልል፣ ከዞን፣ ከከተማና ከወረዳ የተውጣጡ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026