የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኮንስትራክሽን ዘርፍ የልህቀት ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ ነው

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የኮንስትራክሽን ዘርፍ እድገትን ይበልጥ በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት የሚያስችል የልህቀት ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ መሆኑ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) ገለፁ።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የኢትዮጵያ የመሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሣምንት መርሃ ግብር በአዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል።

በዚህም "የግንባታ ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ" በሚል ርዕስ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።


የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የመንገዶች፣ ድልድዮችንና የግድቦች ግንባታን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።

ይህም ሀገሪቱ በግንባታ ሂደት ላይ መሆኗን የሚያመላክት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ እኛ ስንገነባ ሀገር ትገነባለች በሚል እሳቤ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ውስጥ መሠረተ ልማትን በማስፋፋት የኢትዮጵያን ብልፅግና የማረጋገጥ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በግንባታው ሂደት የሚሳተፉ የሀገር ውስጥ የሥራ ተቋራጮችና ኩባንያዎች አቅማቸውን በማሳደግ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን አለባቸው ብለዋል።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ ዘርፉን ዘመናዊ፣ ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ፣ ጠንካራ ቁጥጥርና ክትትል ሥርዓት መዘርጋት እና ተቋማዊ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑ ተናግረዋል።

የዘርፉን ዕድገት በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት የልህቀት ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ መሆኑ ገልፀዋል።

በግንባታው ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መስፍን ነገዎ( ዶ/ር) በፓናል ውይይቱ ባቀረቡት ጽሁፍ ፤በኢትዮጵያ የግንባታ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚታዩ የአሰራር ክፍተቶችን ለመቅረፍ እና ዘርፉን ለማዘመን የተቀናጀ የቁጥጥር ማዕቀፍ እና የዲጂታል አሰራር ሥርዓት መዘርጋት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።


ዘርፉ ለሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ቢሆንም፣ አሁንም ድረስ የቆዩና በእጅ የሚከናወኑ አሰራሮች፣ የተበታተኑ መረጃዎች እና የግልጽነት ማነስ እንደ ዋና ተግዳሮት መቀጠላቸውን አስረድተዋል።

የግንባታው ዘርፍ ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲሸጋገር ፖሊሲዎችን፣ ሕጎችን፣ ደረጃዎችን እና ዲጂታል ቴክኖሎጂን ያጣመረ ሁሉን አቀፍ የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡

የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ቅድስት ማሞ በበኩላቸው፤ የዘርፉን አቅም ለማሳደግ የሰው ኃይል ልማት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና ተቋማዊ አደረጃጀትን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።


የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በአሁኑ ወቅት ወሳኝ በሆነ የለውጥ ምዕራፍ ላይ እንዳለም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026