🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የኮንስትራክሽን ዘርፍ እድገትን ይበልጥ በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት የሚያስችል የልህቀት ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ መሆኑ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) ገለፁ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የኢትዮጵያ የመሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሣምንት መርሃ ግብር በአዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል።
በዚህም "የግንባታ ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ" በሚል ርዕስ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የመንገዶች፣ ድልድዮችንና የግድቦች ግንባታን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
ይህም ሀገሪቱ በግንባታ ሂደት ላይ መሆኗን የሚያመላክት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ እኛ ስንገነባ ሀገር ትገነባለች በሚል እሳቤ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ውስጥ መሠረተ ልማትን በማስፋፋት የኢትዮጵያን ብልፅግና የማረጋገጥ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በግንባታው ሂደት የሚሳተፉ የሀገር ውስጥ የሥራ ተቋራጮችና ኩባንያዎች አቅማቸውን በማሳደግ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን አለባቸው ብለዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ ዘርፉን ዘመናዊ፣ ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ፣ ጠንካራ ቁጥጥርና ክትትል ሥርዓት መዘርጋት እና ተቋማዊ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑ ተናግረዋል።
የዘርፉን ዕድገት በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት የልህቀት ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ መሆኑ ገልፀዋል።
በግንባታው ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መስፍን ነገዎ( ዶ/ር) በፓናል ውይይቱ ባቀረቡት ጽሁፍ ፤በኢትዮጵያ የግንባታ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚታዩ የአሰራር ክፍተቶችን ለመቅረፍ እና ዘርፉን ለማዘመን የተቀናጀ የቁጥጥር ማዕቀፍ እና የዲጂታል አሰራር ሥርዓት መዘርጋት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

ዘርፉ ለሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ቢሆንም፣ አሁንም ድረስ የቆዩና በእጅ የሚከናወኑ አሰራሮች፣ የተበታተኑ መረጃዎች እና የግልጽነት ማነስ እንደ ዋና ተግዳሮት መቀጠላቸውን አስረድተዋል።
የግንባታው ዘርፍ ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲሸጋገር ፖሊሲዎችን፣ ሕጎችን፣ ደረጃዎችን እና ዲጂታል ቴክኖሎጂን ያጣመረ ሁሉን አቀፍ የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡
የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ቅድስት ማሞ በበኩላቸው፤ የዘርፉን አቅም ለማሳደግ የሰው ኃይል ልማት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና ተቋማዊ አደረጃጀትን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በአሁኑ ወቅት ወሳኝ በሆነ የለውጥ ምዕራፍ ላይ እንዳለም ገልፀዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026