የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ መኽር እርሻ ከ11 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ይለማል

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 ዓ.ም (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ የመኽር እርሻ ወቅት ከ11 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የሰብል ልማት ዳይሬክተር አቶ ሙስጠፋ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በመኽር እርሻው ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በዝግጅት ምዕራፍ ላይ ትኩረት ተደርጎ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል።

በክልሉ በሚገኙ 21 ዞኖችና 29 ከተሞች የመኽር እርሻው በስፋት እንደሚከናወን ገልጸው፤ ለስራው ስኬታማነት ከአርሶ አደሮች ጋር ሰፊ የንቅናቄ ውይይት መደረጉን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅትም የመኸር አዝመራ ቀደም ብሎ በሚገባባቸው አካባቢዎች የመሬት ዝግጅት ስራ የተጀመረ ሲሆን ስራውም በሜካናይዜሽን ታግዞ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።


ምርታማነትን ለማሳደግ ግብርናውን ዘመናዊ የማድረግ ስራ ትኩረት እንደተሰጠው ያስታዋሱት ዳይሬክተሩ በዘንድሮ 50 በመቶ የሚሆነውን የእርሻ ስራ በትራክተር ለማከናወን ታቅዷል ነው ያሉት።

በመኽር እርሻ 11 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት የታቀደ ሲሆን ለመኽሩ 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል ምርጥና የተሻሻሉ ምርጥ ዘር ይቀርባል ብለዋል።

ከታቀደው ጠቅላላ መሬት ውስጥ 250 ሺህ ሄክታሩ በከተሞች ስር በሚተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች የሚለማ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ለልማቱ ስኬታማነት አስፈላጊ የሆኑ የግብርና ግብዓቶችን በወቅቱ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል የተሻሻለ ምርጥ ዘር ይቀርባልም ብለዋል።


ለጠቅላላ የእርሻ ስራው 14 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ የታቀደ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት 7 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ በክልሉ ደርሷል ነው ያሉት።

ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታሉ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ያነሱ ሲሆን በዘንድሮው ዓመት በክልሉ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት እንዳይኖር ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።

በክልሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት፤ መስኖ፣ በልግና መኽር እርሻ በስፋት በመተግበሩ ምርትና ምርታማነት በየጊዜው እያደገ መምጣቱንም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026