የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ መኽር እርሻ ከ11 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ይለማል

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 ዓ.ም (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ የመኽር እርሻ ወቅት ከ11 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የሰብል ልማት ዳይሬክተር አቶ ሙስጠፋ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በመኽር እርሻው ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በዝግጅት ምዕራፍ ላይ ትኩረት ተደርጎ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል።

በክልሉ በሚገኙ 21 ዞኖችና 29 ከተሞች የመኽር እርሻው በስፋት እንደሚከናወን ገልጸው፤ ለስራው ስኬታማነት ከአርሶ አደሮች ጋር ሰፊ የንቅናቄ ውይይት መደረጉን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅትም የመኸር አዝመራ ቀደም ብሎ በሚገባባቸው አካባቢዎች የመሬት ዝግጅት ስራ የተጀመረ ሲሆን ስራውም በሜካናይዜሽን ታግዞ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።


ምርታማነትን ለማሳደግ ግብርናውን ዘመናዊ የማድረግ ስራ ትኩረት እንደተሰጠው ያስታዋሱት ዳይሬክተሩ በዘንድሮ 50 በመቶ የሚሆነውን የእርሻ ስራ በትራክተር ለማከናወን ታቅዷል ነው ያሉት።

በመኽር እርሻ 11 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት የታቀደ ሲሆን ለመኽሩ 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል ምርጥና የተሻሻሉ ምርጥ ዘር ይቀርባል ብለዋል።

ከታቀደው ጠቅላላ መሬት ውስጥ 250 ሺህ ሄክታሩ በከተሞች ስር በሚተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች የሚለማ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ለልማቱ ስኬታማነት አስፈላጊ የሆኑ የግብርና ግብዓቶችን በወቅቱ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል የተሻሻለ ምርጥ ዘር ይቀርባልም ብለዋል።


ለጠቅላላ የእርሻ ስራው 14 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ የታቀደ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት 7 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ በክልሉ ደርሷል ነው ያሉት።

ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታሉ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ያነሱ ሲሆን በዘንድሮው ዓመት በክልሉ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት እንዳይኖር ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።

በክልሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት፤ መስኖ፣ በልግና መኽር እርሻ በስፋት በመተግበሩ ምርትና ምርታማነት በየጊዜው እያደገ መምጣቱንም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026