🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ ስራዎች ኢትዮጵያን ለንግድና ለኢንቨስትመንት አጋርነት የምትመረጥ ሀገር እንዳደረጓት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የ100 ቀናት ግምገማና የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ሚኒስትሯ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ መሪዎች ኢትዮጵያን መጎብኘት ችለዋል።

ይህም የተከናወነው የለውጥ ስራ እና በዚህ አማካኝነትም እየመጣ ያለው ለውጥ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ እንደሆነ አስረድተዋል።
አሁን ላይ ኢትዮጵያ ከእርዳታ ይልቅ ለንግድና ለኢንቨስትመንት አጋርነት የምትመረጥ እንዲሁም የመወዳደር አቅሟ ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ገልጸዋል።
ራሳችንን የገለጽንበት መንገድ ኢትዮጵያ ከተረጂነት እይታ ይልቅ ሉአላዊነትን ያረጋገጠች እርዳታ ቢያስፈልጋት እንኳን በራሷ ማሳካት የምትችል መሆኗንም አስረድተዋል።
ሚኒስትሯ አያይዘውም ኢትዮጵያ ከዓለም መዛመድ የምትፈልግው ለንግድና ለኢንቨስትመንት ነው የሚለው ትርክት የራሱን ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
የተሰሩ ስራዎችና የልማት ውጤቶች ማድረግ የመቻል አቅምን በማሳየት ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሃገራት ጋር ያላትን የግንኙነት ገጽታ የቀየሩ መሆኑን አስረድተዋል።
ከአየር ንብረት ለውጥ ዲፕሎማሲና ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ መሪነት አኳያም ከፍ ያሉ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በምታራምደው ፖሊሲና አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በዓየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ በተግባር ያከናወነቻቸው ስራዎች በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃም ያሳየችው የመሪነት ሚና ተጠቃሽ ሃገር እንዳደረጋትም አስረድተዋል።
የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን በተሳካ ሁኔታ ማስተናገድ መቻሏም የራሱን ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ዓለም አቀፉን የዓየር ንብረት ጉባኤ (COP 32 ) እንድታስተናግድ መመረጥ መቻሏም የዚሁ ማሳያ እንደሆነ ጠቁመዋል።
Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ሃገራዊ_ለውጥ
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025