የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ስራዎች ኢትዮጵያን ለንግድና ለኢንቨስትመንት የሚመርጧት ሃገር አድርጓታል - ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ ስራዎች ኢትዮጵያን ለንግድና ለኢንቨስትመንት አጋርነት የምትመረጥ ሀገር እንዳደረጓት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የ100 ቀናት ግምገማና የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ሚኒስትሯ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ መሪዎች ኢትዮጵያን መጎብኘት ችለዋል።


ይህም የተከናወነው የለውጥ ስራ እና በዚህ አማካኝነትም እየመጣ ያለው ለውጥ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ እንደሆነ አስረድተዋል።

አሁን ላይ ኢትዮጵያ ከእርዳታ ይልቅ ለንግድና ለኢንቨስትመንት አጋርነት የምትመረጥ እንዲሁም የመወዳደር አቅሟ ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ገልጸዋል።

ራሳችንን የገለጽንበት መንገድ ኢትዮጵያ ከተረጂነት እይታ ይልቅ ሉአላዊነትን ያረጋገጠች እርዳታ ቢያስፈልጋት እንኳን በራሷ ማሳካት የምትችል መሆኗንም አስረድተዋል።

ሚኒስትሯ አያይዘውም ኢትዮጵያ ከዓለም መዛመድ የምትፈልግው ለንግድና ለኢንቨስትመንት ነው የሚለው ትርክት የራሱን ሚና ተጫውቷል ብለዋል።

የተሰሩ ስራዎችና የልማት ውጤቶች ማድረግ የመቻል አቅምን በማሳየት ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሃገራት ጋር ያላትን የግንኙነት ገጽታ የቀየሩ መሆኑን አስረድተዋል።

ከአየር ንብረት ለውጥ ዲፕሎማሲና ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ መሪነት አኳያም ከፍ ያሉ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በምታራምደው ፖሊሲና አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በዓየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ በተግባር ያከናወነቻቸው ስራዎች በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃም ያሳየችው የመሪነት ሚና ተጠቃሽ ሃገር እንዳደረጋትም አስረድተዋል።

የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን በተሳካ ሁኔታ ማስተናገድ መቻሏም የራሱን ሚና ተጫውቷል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ዓለም አቀፉን የዓየር ንብረት ጉባኤ (COP 32 ) እንድታስተናግድ መመረጥ መቻሏም የዚሁ ማሳያ እንደሆነ ጠቁመዋል።

Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ሃገራዊ_ለውጥ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025