የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ስራዎች ኢትዮጵያን ለንግድና ለኢንቨስትመንት የሚመርጧት ሃገር አድርጓታል - ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ ስራዎች ኢትዮጵያን ለንግድና ለኢንቨስትመንት አጋርነት የምትመረጥ ሀገር እንዳደረጓት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የ100 ቀናት ግምገማና የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ሚኒስትሯ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ መሪዎች ኢትዮጵያን መጎብኘት ችለዋል።


ይህም የተከናወነው የለውጥ ስራ እና በዚህ አማካኝነትም እየመጣ ያለው ለውጥ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ እንደሆነ አስረድተዋል።

አሁን ላይ ኢትዮጵያ ከእርዳታ ይልቅ ለንግድና ለኢንቨስትመንት አጋርነት የምትመረጥ እንዲሁም የመወዳደር አቅሟ ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ገልጸዋል።

ራሳችንን የገለጽንበት መንገድ ኢትዮጵያ ከተረጂነት እይታ ይልቅ ሉአላዊነትን ያረጋገጠች እርዳታ ቢያስፈልጋት እንኳን በራሷ ማሳካት የምትችል መሆኗንም አስረድተዋል።

ሚኒስትሯ አያይዘውም ኢትዮጵያ ከዓለም መዛመድ የምትፈልግው ለንግድና ለኢንቨስትመንት ነው የሚለው ትርክት የራሱን ሚና ተጫውቷል ብለዋል።

የተሰሩ ስራዎችና የልማት ውጤቶች ማድረግ የመቻል አቅምን በማሳየት ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሃገራት ጋር ያላትን የግንኙነት ገጽታ የቀየሩ መሆኑን አስረድተዋል።

ከአየር ንብረት ለውጥ ዲፕሎማሲና ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ መሪነት አኳያም ከፍ ያሉ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በምታራምደው ፖሊሲና አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በዓየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ በተግባር ያከናወነቻቸው ስራዎች በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃም ያሳየችው የመሪነት ሚና ተጠቃሽ ሃገር እንዳደረጋትም አስረድተዋል።

የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን በተሳካ ሁኔታ ማስተናገድ መቻሏም የራሱን ሚና ተጫውቷል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ዓለም አቀፉን የዓየር ንብረት ጉባኤ (COP 32 ) እንድታስተናግድ መመረጥ መቻሏም የዚሁ ማሳያ እንደሆነ ጠቁመዋል።

Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ሃገራዊ_ለውጥ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026