🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ ስራዎች ኢትዮጵያን ለንግድና ለኢንቨስትመንት አጋርነት የምትመረጥ ሀገር እንዳደረጓት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የ100 ቀናት ግምገማና የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ሚኒስትሯ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ መሪዎች ኢትዮጵያን መጎብኘት ችለዋል።

ይህም የተከናወነው የለውጥ ስራ እና በዚህ አማካኝነትም እየመጣ ያለው ለውጥ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ እንደሆነ አስረድተዋል።
አሁን ላይ ኢትዮጵያ ከእርዳታ ይልቅ ለንግድና ለኢንቨስትመንት አጋርነት የምትመረጥ እንዲሁም የመወዳደር አቅሟ ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ገልጸዋል።
ራሳችንን የገለጽንበት መንገድ ኢትዮጵያ ከተረጂነት እይታ ይልቅ ሉአላዊነትን ያረጋገጠች እርዳታ ቢያስፈልጋት እንኳን በራሷ ማሳካት የምትችል መሆኗንም አስረድተዋል።
ሚኒስትሯ አያይዘውም ኢትዮጵያ ከዓለም መዛመድ የምትፈልግው ለንግድና ለኢንቨስትመንት ነው የሚለው ትርክት የራሱን ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
የተሰሩ ስራዎችና የልማት ውጤቶች ማድረግ የመቻል አቅምን በማሳየት ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሃገራት ጋር ያላትን የግንኙነት ገጽታ የቀየሩ መሆኑን አስረድተዋል።
ከአየር ንብረት ለውጥ ዲፕሎማሲና ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ መሪነት አኳያም ከፍ ያሉ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በምታራምደው ፖሊሲና አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በዓየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ በተግባር ያከናወነቻቸው ስራዎች በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃም ያሳየችው የመሪነት ሚና ተጠቃሽ ሃገር እንዳደረጋትም አስረድተዋል።
የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን በተሳካ ሁኔታ ማስተናገድ መቻሏም የራሱን ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ዓለም አቀፉን የዓየር ንብረት ጉባኤ (COP 32 ) እንድታስተናግድ መመረጥ መቻሏም የዚሁ ማሳያ እንደሆነ ጠቁመዋል።
Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ሃገራዊ_ለውጥ
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026