የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ በመሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ በመሆን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነች እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ገለፀ።

በባህር ዳር ከተማ ''የብሪክስ አሁናዊ አቅሞች እና የኢትዮጵያ የልማት ትብብር ትኩረቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ጉባኤ መካሔድ ጀምሯል።

የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሐመድራፊዕ አባራያ በመድረኩ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በብሪክስ አባልነቷ ንቁ ተሳትፎ እያደረገች ትገኛለች።

በዚህም ተሳትፎዋን በማሳደግ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የተደራጁ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ገልፀዋል።

የብሪክስ ሚና እየጎላ መምጣቱን ጠቅሰው በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ አለም አቀፋዊ አቅሞችን በማስተባበር እየገጠሙ የሚገኙ ችግሮች በትብብር መፍትሄ ያገኛሉ ብለዋል።

በማዕቀፉም ኢትዮጵያ የመፍትሄ ሀሳብ አፍላቂ በመሆን ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ እየተሳተፈች እንደምትገኝ አመልክተዋል።

መድረኩ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችላት የሁለትዮሽ ትብብር ጭምር የሚካሄድበት መሆኑንም አስረድተዋል።

የብሪክስ ማዕቀፋ በተለይም በግብርና እና ስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና መሰል ዘርፎች ልምድ የሚሰጥበትና የሚገኝበት መድረክ መሆኑንም አንስተዋል።

በጉባኤው የኢትዮጵያ የ2025 የብሪክስ ተሳትፎ እና ቀጣይ አገራዊ ትኩረቶች፣ የኢትዮጵያ የአካዳሚክ ምርምርና አሰላሳይ ተቋማት ትኩረት ከሚደረግባቸው መስኮች ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።


በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የማህበራዊ ፖሊሲ ዋና አማካሪ አምባሳደር ሚኒልክ አለሙ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገራት አንዷ መሆኗ ቁልፍና መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።

ብሪክስ የዓለምን ህዝብ 50 በመቶ፤ የዓለምን ኢኮኖሚ ደግሞ 40 በመቶ የሚሸፍን መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ በመነሳት ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቷን ታረጋግጣለች ነው ያሉት።

ብሪክስ የማይበገርና ዘላቂነት ያለው የትብብር ማእቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፣ የኢትዮጵያን በባለብዙ ዘርፍ ዲፕሎማሲ በማሳተፍ ተጠቃሚነቷን ብሎም ተሰሚነቷን ያሳድጋል ብለዋል።

ይኸው ጉባኤ ለፖሊሲ አውጪዎችና ለሌሎች ጠቀሜታ የሚውል የመፍትሔ ሀሳብ ማፍለቂያ መድረክ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026