🔇Unmute
ባህርዳር፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ በመሆን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነች እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ገለፀ።
በባህር ዳር ከተማ ''የብሪክስ አሁናዊ አቅሞች እና የኢትዮጵያ የልማት ትብብር ትኩረቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ጉባኤ መካሔድ ጀምሯል።
የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሐመድራፊዕ አባራያ በመድረኩ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በብሪክስ አባልነቷ ንቁ ተሳትፎ እያደረገች ትገኛለች።
በዚህም ተሳትፎዋን በማሳደግ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የተደራጁ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ገልፀዋል።
የብሪክስ ሚና እየጎላ መምጣቱን ጠቅሰው በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ አለም አቀፋዊ አቅሞችን በማስተባበር እየገጠሙ የሚገኙ ችግሮች በትብብር መፍትሄ ያገኛሉ ብለዋል።
በማዕቀፉም ኢትዮጵያ የመፍትሄ ሀሳብ አፍላቂ በመሆን ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ እየተሳተፈች እንደምትገኝ አመልክተዋል።
መድረኩ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችላት የሁለትዮሽ ትብብር ጭምር የሚካሄድበት መሆኑንም አስረድተዋል።
የብሪክስ ማዕቀፋ በተለይም በግብርና እና ስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና መሰል ዘርፎች ልምድ የሚሰጥበትና የሚገኝበት መድረክ መሆኑንም አንስተዋል።
በጉባኤው የኢትዮጵያ የ2025 የብሪክስ ተሳትፎ እና ቀጣይ አገራዊ ትኩረቶች፣ የኢትዮጵያ የአካዳሚክ ምርምርና አሰላሳይ ተቋማት ትኩረት ከሚደረግባቸው መስኮች ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የማህበራዊ ፖሊሲ ዋና አማካሪ አምባሳደር ሚኒልክ አለሙ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገራት አንዷ መሆኗ ቁልፍና መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።
ብሪክስ የዓለምን ህዝብ 50 በመቶ፤ የዓለምን ኢኮኖሚ ደግሞ 40 በመቶ የሚሸፍን መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ በመነሳት ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቷን ታረጋግጣለች ነው ያሉት።
ብሪክስ የማይበገርና ዘላቂነት ያለው የትብብር ማእቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፣ የኢትዮጵያን በባለብዙ ዘርፍ ዲፕሎማሲ በማሳተፍ ተጠቃሚነቷን ብሎም ተሰሚነቷን ያሳድጋል ብለዋል።
ይኸው ጉባኤ ለፖሊሲ አውጪዎችና ለሌሎች ጠቀሜታ የሚውል የመፍትሔ ሀሳብ ማፍለቂያ መድረክ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመላክተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026