የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ደብረ ብርሀን ከተማ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማዕከል እየሆነች ነው

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ደብረ ብርሃን ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የከተማው ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት አስታወቁ።

በአትሌት ሻለቃ ሃይሌ ገብረስላሴ በ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ወጪ በደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባው ባለ 4 ኮከብ ዘመናዊ ሆቴል ዛሬ ተመርቋል።


ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ በድሉ ውብሸት በሆቴሉ ምረቃ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት፤ የደብረ ብርሃን ከተማ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማዕከል እየሆነች መጥታለች።


ዛሬ የተመረቀው ባለ 4 ኮከብ ዘመናዊ ሆቴልም ከተማዋ ታላላቅ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ኮንፈረንሶችን ለማስተናገድ ተመራጭ እንድትሆን የሚያስችላት መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በከተማዋም ሆነ በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ቅርሶችን ለመጎብኘት የሚመጡ ቱሪስቶች ቁጥር እንዲጨምር ያግዛል ብለዋል፡፡

ሆቴሉ ለከተማዋ ወጣቶች ተጨማሪ የሥራ ዕድል የሚፈጥርና የከተማዋን ገጽታ የሚገነባ መሆኑን ጠቁመው የከተማ አስተዳደሩ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በበኩላቸው፤ ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ በአትሌትነት ጊዜው "የይቻላል" መንፈስን ለኢትዮጵያውያን ወጣቶች ያስተማረ ጀግና ነው ብለዋል።


በደብረብርሃን ከተማ ያስገነባው ሆቴል ዞኑን የቱሪዝም፣ የኢንዱስትሪና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል።

የሃይሌ እና ዓለም፤ ዓለም አቀፍ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ግሩፕ ባለቤት አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ እንደገለጸው፤ በሆቴልና ሪዞርት ዘርፍ ኢትዮጵያ ፈጣን እድገት እንድታስመዘግብ የበኩሉን እየተወጣ ነው።

ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ በ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ተገንብቶ የተመረቀው ባለ 4 ኮከብ ሆቴልም የድርጅቱን የሆቴሎችና ሪዞርቶች ቁጥር ወደ 11 በማሳደግ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆን ያስችላል ብሏል።


ሆቴሉ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ መገንባቱንና ዘመናዊ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የተሟላ ጂምናዚየም እና ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን እንዲሰጥ ተደርጎ የተገነባ መሆኑን አብራርቷል።

ሆቴሉ በአሁኑ ወቅት ለ200 ዜጎች ቋሚ የሥራ እድል የፈጠረ ሲሆን በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባ የሥራ እድል ተጠቃሚዎችን ቁጥር ከ300 በላይ እንደሚሆንም አመልክቷል።

በቀጣይም በጎንደር፣ በሐረር እና በድሬዳዋ ከተሞች አዳዲስ መዳረሻዎች በማስገንባት በዘርፉ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026