የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ደብረ ብርሀን ከተማ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማዕከል እየሆነች ነው

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ደብረ ብርሃን ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የከተማው ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት አስታወቁ።

በአትሌት ሻለቃ ሃይሌ ገብረስላሴ በ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ወጪ በደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባው ባለ 4 ኮከብ ዘመናዊ ሆቴል ዛሬ ተመርቋል።


ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ በድሉ ውብሸት በሆቴሉ ምረቃ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት፤ የደብረ ብርሃን ከተማ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማዕከል እየሆነች መጥታለች።


ዛሬ የተመረቀው ባለ 4 ኮከብ ዘመናዊ ሆቴልም ከተማዋ ታላላቅ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ኮንፈረንሶችን ለማስተናገድ ተመራጭ እንድትሆን የሚያስችላት መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በከተማዋም ሆነ በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ቅርሶችን ለመጎብኘት የሚመጡ ቱሪስቶች ቁጥር እንዲጨምር ያግዛል ብለዋል፡፡

ሆቴሉ ለከተማዋ ወጣቶች ተጨማሪ የሥራ ዕድል የሚፈጥርና የከተማዋን ገጽታ የሚገነባ መሆኑን ጠቁመው የከተማ አስተዳደሩ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በበኩላቸው፤ ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ በአትሌትነት ጊዜው "የይቻላል" መንፈስን ለኢትዮጵያውያን ወጣቶች ያስተማረ ጀግና ነው ብለዋል።


በደብረብርሃን ከተማ ያስገነባው ሆቴል ዞኑን የቱሪዝም፣ የኢንዱስትሪና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል።

የሃይሌ እና ዓለም፤ ዓለም አቀፍ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ግሩፕ ባለቤት አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ እንደገለጸው፤ በሆቴልና ሪዞርት ዘርፍ ኢትዮጵያ ፈጣን እድገት እንድታስመዘግብ የበኩሉን እየተወጣ ነው።

ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ በ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ተገንብቶ የተመረቀው ባለ 4 ኮከብ ሆቴልም የድርጅቱን የሆቴሎችና ሪዞርቶች ቁጥር ወደ 11 በማሳደግ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆን ያስችላል ብሏል።


ሆቴሉ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ መገንባቱንና ዘመናዊ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የተሟላ ጂምናዚየም እና ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን እንዲሰጥ ተደርጎ የተገነባ መሆኑን አብራርቷል።

ሆቴሉ በአሁኑ ወቅት ለ200 ዜጎች ቋሚ የሥራ እድል የፈጠረ ሲሆን በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባ የሥራ እድል ተጠቃሚዎችን ቁጥር ከ300 በላይ እንደሚሆንም አመልክቷል።

በቀጣይም በጎንደር፣ በሐረር እና በድሬዳዋ ከተሞች አዳዲስ መዳረሻዎች በማስገንባት በዘርፉ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026