🔇Unmute
አርባምንጭ፤ ሚያዝያ 15/2018 (ኢዜአ)፡- አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ እድገቱ የሚያበረክተውን ሚና ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሠ መሥተዳድርና የሥራና ክኅሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሠ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።
ክልል አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር በአርባ ምንጭ ከተማ የተከፈተ ሲሆን፤ የፓናል ውይይትም ተካሂዷል።

አበባየሁ ታደሠ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ አምራች ኢንዱስትሪው ተኪ ምርት ከማምረት አንፃር ያለውን ሚና ለማጉላት በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ እድገቱ የሚያበረክተውን ሚና ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን አረጋግጠዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴዔታ ታረቀኝ ቡሉልታ በበኩላቸው፤ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሙሉ ዐቅማቸው እንዲያመርቱ የፋይናንስና የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የገበያ ችግሮችን ለመፍታት ሁለንተናዊ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ልማትን በማፋጠን ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ በመገንባት ጠንካራ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለመፍጠር በቅንጅት እየተሠራ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ሰለሞን ናቸው።

ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከ3 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 30 ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቅሰው፤ ለ27 ሺህ 817 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም አስረድተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026