የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ እድገቱ የሚያበረክተውን ሚና ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቷል

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባምንጭ፤ ሚያዝያ 15/2018 (ኢዜአ)፡- አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ እድገቱ የሚያበረክተውን ሚና ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሠ መሥተዳድርና የሥራና ክኅሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሠ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።

ክልል አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር በአርባ ምንጭ ከተማ የተከፈተ ሲሆን፤ የፓናል ውይይትም ተካሂዷል።


አበባየሁ ታደሠ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ አምራች ኢንዱስትሪው ተኪ ምርት ከማምረት አንፃር ያለውን ሚና ለማጉላት በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ እድገቱ የሚያበረክተውን ሚና ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን አረጋግጠዋል።


የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴዔታ ታረቀኝ ቡሉልታ በበኩላቸው፤ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሙሉ ዐቅማቸው እንዲያመርቱ የፋይናንስና የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የገበያ ችግሮችን ለመፍታት ሁለንተናዊ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

የኢንዱስትሪ ልማትን በማፋጠን ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ በመገንባት ጠንካራ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለመፍጠር በቅንጅት እየተሠራ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ሰለሞን ናቸው።


ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከ3 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 30 ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቅሰው፤ ለ27 ሺህ 817 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026