የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሃ ግብሮች የተገነቡ የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ናቸው

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሃ ግብሮች የተገነቡ የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ መሆናቸውን የቱሪዝም ሚኒስትር ሠላማዊት ካሳ ገለጹ፡፡

በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም ሀብቶችን ለማልማት በቅንጅት እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 17ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።

በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ አንቀጽ 92 መሠረት የቱሪዝም ሚኒስትር ሠላማዊት ካሳ በምክር ቤቱ ተገኝተው ከአባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።


በውይይቱ ላይ አባላቱ በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሃ ግብሮች የተገነቡ አዳዲስ መዳረሻዎችን በማልማት የቱሪዝም ዲፕሎማሲን እና የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ለማጠናከር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማና አበረታች ናቸው ብለዋል፡፡

እነዚህ ሥራዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአካባቢ ጸጋዎችን ለይተው ወደ ሀብት ለመቀየር ያላቸውን ልዩ ክህሎትና ብቃት የሚያሳዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ሀገራዊ የቱሪዝም መስህቦችን በመመዝገብ ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን የሚመለከትም ጥያቄ ቀርቧል።

ሚኒስትሯ በሰጡት ማብራሪያ፤ መንግሥት ቱሪዝምን አንዱ የኢኮኖሚ ምሶሶ በማድረግ የመዳረሻ ልማትን ጨምሮ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነት በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች በርካታ የቱሪዝም ስፍራዎችና መዳረሻዎች መገንባታቸውን ጠቅሰዋል።

እነዚህ የልማት ሥራዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የመስህብ ምዝገባ ሂደትን በተመለከተም በሰጡት ማብራሪያም አበረታች በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው እስካሁንም 800 የሚሆኑ የቱሪስት መስህቦች መመዝገባቸውን ይፋ አድርገዋል።

በተጨማሪም ሀገር አቀፍ የቱሪዝም ካርታ በማዘጋጀት ረገድ በሲዳማ ክልል የተከናወነው የናሙና ሥራ በስኬት መጠናቀቁን ጠቅሰው ይህንን በመላ ሀገሪቱ የማከናወን ስራ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ጠቁምዋል፡፡

የግሉ ሴክተር በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም ሃብቶችን በማልማት ሂደት ያላቸዉን ተሳትፎ ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

እንዲሁም የማህበረሰቡን አቅም በማስተባበር የማልማት ስራ እና ደረጃቸውን ከፍ የማድረግ ስራዎች እንደሚሰሩም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026