የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሃ ግብሮች የተገነቡ የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ናቸው

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሃ ግብሮች የተገነቡ የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ መሆናቸውን የቱሪዝም ሚኒስትር ሠላማዊት ካሳ ገለጹ፡፡

በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም ሀብቶችን ለማልማት በቅንጅት እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 17ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።

በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ አንቀጽ 92 መሠረት የቱሪዝም ሚኒስትር ሠላማዊት ካሳ በምክር ቤቱ ተገኝተው ከአባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።


በውይይቱ ላይ አባላቱ በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሃ ግብሮች የተገነቡ አዳዲስ መዳረሻዎችን በማልማት የቱሪዝም ዲፕሎማሲን እና የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ለማጠናከር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማና አበረታች ናቸው ብለዋል፡፡

እነዚህ ሥራዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአካባቢ ጸጋዎችን ለይተው ወደ ሀብት ለመቀየር ያላቸውን ልዩ ክህሎትና ብቃት የሚያሳዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ሀገራዊ የቱሪዝም መስህቦችን በመመዝገብ ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን የሚመለከትም ጥያቄ ቀርቧል።

ሚኒስትሯ በሰጡት ማብራሪያ፤ መንግሥት ቱሪዝምን አንዱ የኢኮኖሚ ምሶሶ በማድረግ የመዳረሻ ልማትን ጨምሮ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነት በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች በርካታ የቱሪዝም ስፍራዎችና መዳረሻዎች መገንባታቸውን ጠቅሰዋል።

እነዚህ የልማት ሥራዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የመስህብ ምዝገባ ሂደትን በተመለከተም በሰጡት ማብራሪያም አበረታች በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው እስካሁንም 800 የሚሆኑ የቱሪስት መስህቦች መመዝገባቸውን ይፋ አድርገዋል።

በተጨማሪም ሀገር አቀፍ የቱሪዝም ካርታ በማዘጋጀት ረገድ በሲዳማ ክልል የተከናወነው የናሙና ሥራ በስኬት መጠናቀቁን ጠቅሰው ይህንን በመላ ሀገሪቱ የማከናወን ስራ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ጠቁምዋል፡፡

የግሉ ሴክተር በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም ሃብቶችን በማልማት ሂደት ያላቸዉን ተሳትፎ ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

እንዲሁም የማህበረሰቡን አቅም በማስተባበር የማልማት ስራ እና ደረጃቸውን ከፍ የማድረግ ስራዎች እንደሚሰሩም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026