የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል የህዝቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት የሚተገበሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ የህዝቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመንግስትና በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ትብብር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ።

የክልሉ ገንዘብ ቢሮ የመንግስትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ዓመታዊ የአጋርነት የምክክር መድረክ በባህር ዳር ከተማ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።


ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለጹት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚጠበቅባቸውን የልማት አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ምቹ ፖሊሲና አሰራር ተቀርጾ ተግበራዊ ተደርጓል።

ድርጅቶቹ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች፣ በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና በሰብዓዊ ድጋፍ እያበረከቱ ያለው አስተዋጽኦ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።


ድርጅቶቹ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ተጠቅመው የመንግስትን የልማት አቅጣጫ መሰረት በማድረግ በድህነት ቅነሳና የተለያዩ ችግሮችን በመፍታት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።

የማህበረሰብ ድርጅቶቹ በሚያከናውኑት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተገቢውን ድጋፍና ጥበቃ እንደሚደረግም አመልክተዋል።


የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን በበኩላቸው፤ በክልሉ በርካታ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በተለያዩ የልማት ዘርፎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ቢሮው የልማት አጋሮች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡና የሚያጋጥሟቸውን የአሰራር ክፍተቶች እንዲሞላም የአዋጅና የመመሪያ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የምክክር መደረኩ ዋና ዓላማም በመንግስትና በአጋር ድርጅቶች መካከል የአሰራር ግልጸኝነትና ተጠያቂነት በመፍጠር በቅንጅት ለመስራት ያለመ ነው ብለዋል።

በቢሮው የሲቪል ልማት ድርጅቶች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ አዝመራው ተጫነ እንዳሉት፤ በክልሉ ያሉ 170 የማህበረሰብ ድርጅቶች ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ እየሰሩ ይገኛሉ።


በዚህም የክልሉን ማህበረሰብ የሚጠቅሙ የግብርና፣ የጤና፣ የትምህርት፣ የንጹህ መጠጥ ውሃና ሌሎች የልማት ዘርፎች ከ350 በላይ ፕሮጀክቶችን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ አብራርተዋል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው የምክክርና የልማት ስራዎች ኤግዚቢሽን ማጠናቀቂያ ላይም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ 25 ድርጅቶች ልዩ እውቅናና ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026