የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል የህዝቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት የሚተገበሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ የህዝቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመንግስትና በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ትብብር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ።

የክልሉ ገንዘብ ቢሮ የመንግስትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ዓመታዊ የአጋርነት የምክክር መድረክ በባህር ዳር ከተማ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።


ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለጹት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚጠበቅባቸውን የልማት አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ምቹ ፖሊሲና አሰራር ተቀርጾ ተግበራዊ ተደርጓል።

ድርጅቶቹ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች፣ በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና በሰብዓዊ ድጋፍ እያበረከቱ ያለው አስተዋጽኦ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።


ድርጅቶቹ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ተጠቅመው የመንግስትን የልማት አቅጣጫ መሰረት በማድረግ በድህነት ቅነሳና የተለያዩ ችግሮችን በመፍታት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።

የማህበረሰብ ድርጅቶቹ በሚያከናውኑት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተገቢውን ድጋፍና ጥበቃ እንደሚደረግም አመልክተዋል።


የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን በበኩላቸው፤ በክልሉ በርካታ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በተለያዩ የልማት ዘርፎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ቢሮው የልማት አጋሮች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡና የሚያጋጥሟቸውን የአሰራር ክፍተቶች እንዲሞላም የአዋጅና የመመሪያ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የምክክር መደረኩ ዋና ዓላማም በመንግስትና በአጋር ድርጅቶች መካከል የአሰራር ግልጸኝነትና ተጠያቂነት በመፍጠር በቅንጅት ለመስራት ያለመ ነው ብለዋል።

በቢሮው የሲቪል ልማት ድርጅቶች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ አዝመራው ተጫነ እንዳሉት፤ በክልሉ ያሉ 170 የማህበረሰብ ድርጅቶች ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ እየሰሩ ይገኛሉ።


በዚህም የክልሉን ማህበረሰብ የሚጠቅሙ የግብርና፣ የጤና፣ የትምህርት፣ የንጹህ መጠጥ ውሃና ሌሎች የልማት ዘርፎች ከ350 በላይ ፕሮጀክቶችን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ አብራርተዋል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው የምክክርና የልማት ስራዎች ኤግዚቢሽን ማጠናቀቂያ ላይም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ 25 ድርጅቶች ልዩ እውቅናና ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026