የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ኦሞ-ቱርካና የተሰኘ የምርምር ማዕከል ለማቋቋም የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ ነው

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ግንቦት 4/2018 (ኢዜአ):-ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ኦሞ-ቱርካና የተሰኘ የምርምር ማዕከል ለማቋቋም የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

ከምስራቅ አፍሪካ የምርምር ማዕከላት፣ ከኢጋድ፣ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ከመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስቴር የተውጣጡና ሌሎችም በተገኙበት የ''ኦሞ-ቱርካና የምርምር ማዕከል" ለማቋቋም የሚያስችል የምክክር መድረክ ዛሬ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ተስፋዬ አለሙ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው ባሻገር በጥናትና ምርምር ለማህበረሰብ ለውጥና ተጠቃሚነት እየሰራ ይገኛል።

ይህን ስራውን ለማጠናከር በኦሞ ወንዝና በቱርካና ኃይቅ አቅራቢያ ዩኒቨርሲቲው የ''ኦሞ-ቱርካና የምርምር ማዕከል'' ሊገነባ መሆኑን አስታውቀዋል።

ማዕከሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር ከመፍታት አልፎ በምስራቅ አፍሪካ ለሚከሰቱ ችግሮች በሳይንሳዊ ጥናት የታገዘ መፍትሔ መስጠት እንደሚያስችል ጠቅሰዋል፡፡

የምርምር ማዕከሉ በኦሞ ሸለቆ ያለውን ዕምቅ የብዝሃ ህይወት አቅም አውጥቶ ለመጠቀም እና ሳይንሳዊ ምርምሮችን ለማካሄድ ጭምር ያግዛል ብለዋል።

በዳሰነች ወረዳ ሁለት ሄክታር መሬት ላይ በሚቋቋማው በዚህ ማዕከል ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ከሀገራት የምርምር ማዕከላትና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት ለችግሮች የጋራ መፍትሔ ይመነጭበታልም ተብሏል።

የምርምር ማዕከሉ ግንባታ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር የገለጹት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ግንባታው የሚከናወንበትን ቦታ ከማመቻቸት ጀምሮ በቂ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።

የጂንካ ዩኒቨርሲቲ በእንስሳትና ዓሣ ሀብት፣ በብዝሃ-ህይወት፣ በብዝሃ-ባህል እንዲሁም በአግሮ ኢንዱስትሪ ላይ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ማዕከሉም በእዚህ ዘርፎች ለውጥ ማምጣት የሚያስችል የምርምር ውጤቶች የሚፈልቁበት ይሆናልም ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026