የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ኦሞ-ቱርካና የተሰኘ የምርምር ማዕከል ለማቋቋም የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ ነው

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ግንቦት 4/2018 (ኢዜአ):-ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ኦሞ-ቱርካና የተሰኘ የምርምር ማዕከል ለማቋቋም የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

ከምስራቅ አፍሪካ የምርምር ማዕከላት፣ ከኢጋድ፣ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ከመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስቴር የተውጣጡና ሌሎችም በተገኙበት የ''ኦሞ-ቱርካና የምርምር ማዕከል" ለማቋቋም የሚያስችል የምክክር መድረክ ዛሬ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ተስፋዬ አለሙ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው ባሻገር በጥናትና ምርምር ለማህበረሰብ ለውጥና ተጠቃሚነት እየሰራ ይገኛል።

ይህን ስራውን ለማጠናከር በኦሞ ወንዝና በቱርካና ኃይቅ አቅራቢያ ዩኒቨርሲቲው የ''ኦሞ-ቱርካና የምርምር ማዕከል'' ሊገነባ መሆኑን አስታውቀዋል።

ማዕከሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር ከመፍታት አልፎ በምስራቅ አፍሪካ ለሚከሰቱ ችግሮች በሳይንሳዊ ጥናት የታገዘ መፍትሔ መስጠት እንደሚያስችል ጠቅሰዋል፡፡

የምርምር ማዕከሉ በኦሞ ሸለቆ ያለውን ዕምቅ የብዝሃ ህይወት አቅም አውጥቶ ለመጠቀም እና ሳይንሳዊ ምርምሮችን ለማካሄድ ጭምር ያግዛል ብለዋል።

በዳሰነች ወረዳ ሁለት ሄክታር መሬት ላይ በሚቋቋማው በዚህ ማዕከል ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ከሀገራት የምርምር ማዕከላትና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት ለችግሮች የጋራ መፍትሔ ይመነጭበታልም ተብሏል።

የምርምር ማዕከሉ ግንባታ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር የገለጹት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ግንባታው የሚከናወንበትን ቦታ ከማመቻቸት ጀምሮ በቂ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።

የጂንካ ዩኒቨርሲቲ በእንስሳትና ዓሣ ሀብት፣ በብዝሃ-ህይወት፣ በብዝሃ-ባህል እንዲሁም በአግሮ ኢንዱስትሪ ላይ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ማዕከሉም በእዚህ ዘርፎች ለውጥ ማምጣት የሚያስችል የምርምር ውጤቶች የሚፈልቁበት ይሆናልም ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026