🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ)፡- የሀገር ውስጥ ምርትን በራስ አቅም ማሳደግ የኢኮኖሚ ነጻነታችን እና የሉዓላዊነታችን መሰረት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በጋሞ ዞን የሚገኘውን እና ነሐሴ 2017 ዓ.ም ላይ ሥራ የጀመረውን 'ዮ ሆልዲንግ’ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ መጎብኘታቸውን አስታውቀዋል።

ፋብሪካው የኢንዱስትሪዎቻችንን ፍላጎት በሀገር ውስጥ በመተካት ከውጭ የሚገባ ምርትን ያስቀረ መሆኑን ገልጸዋል።
ለአካባቢው ነዋሪዎችም የሥራ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል በመልዕክታቸው።

የሀገር ውስጥ ምርትን በራስ አቅም ማሳደግ የኢኮኖሚ ነጻነታችን እና የሉዓላዊነታችን መሰረት ነው ሲሉም አስገንዝበዋል።
የሀገራችንን የተፈጥሮ ሀብት በጠንካራ ስራ በሀገር ውስጥ በማልማት የኢኮኖሚ ልዕልናችንን የምናረጋግጥበት ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 4, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026